1 Korinćanima 5 – CRO & NASV

Knijga O Kristu

1 Korinćanima 5:1-13

Pavao osuđuje uznositost zbog duhovnosti

1Pročulo se o takvom bludu među vama, o takvom zlu kakvo čak ni pogani ne čine. Kažu mi da neki čovjek iz vaše crkve živi u grijehu sa ženom svojega oca. 2A vi ste se još umislili. Zašto niste u žalosti? Uklonite iz svojega zajedništva počinitelja tog nedjela.

3Iako nisam nazočan tijelom, nazočan sam duhom te sam presudio, kao da sam s vama, čovjeku koji je takvo što počinio: 4okupite Crkvu u ime našega Gospodina Isusa Krista. Ja ću biti s vama duhom, kao i sila Gospodina Isusa. 5Predajte toga čovjeka Sotoni u ruke: isključite ga iz Crkve da trpi u tijelu5:5 U grčkome: na propast tijela. kako bi se on5:5 U grčkome: njegov duh. spasio na dan Gospodina Isusa.

6Kako se još možete hvaliti! Kao da ne znate da malo kvasca ukvasi sve tijesto! Dopustite li jednomu da griješi, ubrzo će se grijeh proširiti. 7Očistite se od staroga kvasca da budete novo tijesto, kao što i jeste beskvasni, jer je naše pashalno janje—Krist—već žrtvovano. 8Svetkujmo zato blagdan, ne sa starim kvascem niti s kvascem zloće i pokvarenosti, već s beskvasnim kruhom čistoće i čestitosti.

9U prijašnjoj sam vam poslanici napisao da se ne družite s bludnicima. 10Nisam pri tome mislio na bludnike općenito, na nevjernike iz svijeta koji su bludnici, ili lakomci, ili varalice, ili idolopoklonici—jer inače biste morali izići iz svijeta. 11Mislio sam da se ne družite s ljudima koji sebe nazivaju kršćanima,5:11 U grčkome: braćom. a bludnici su, ili lakomci, ili idolopoklonici, ili klevetnici, ili pijanci, ili varalice.

12Nije na meni da sudim one koji su vani. Ali onima u Crkvi koji tako griješe trebate suditi. 13Onima koji su vani sudit će Bog. Ali u Svetome pismu piše: “Isključite opakoga iz svoje sredine.”

New Amharic Standard Version

1 ቆሮንቶስ 5:1-13

አሳፋሪ ኀጢአት በቤተ ክርስቲያን

1በመካከላችሁ የዝሙት ርኩሰት እንዳለ በርግጥ ይወራል፤ እንዲህ ያለው ርኩሰት በአረማውያን ዘንድ እንኳ ታይቶ የማይታወቅ ነው፤ የአባቱን ሚስት ያገባ ሰው አለና። 2ደግሞም ታብያችኋል! ይልቅስ ሐዘን ተሰምቷችሁ፣ ይህን ድርጊት የፈጸመውን ሰው ከመካከላችሁ ልታስወግዱት አይገባምን? 3ምንም እንኳ እኔ በአካል አብሬያችሁ ባልሆንም፣ በመንፈስ ግን ከእናንተ ጋር ነኝ፤ ልክ አብሬያችሁ እንዳለሁ ሆኜ፣ ይህን ባደረገው ሰው ላይ አሁኑኑ ፈርጄበታለሁ። 4በምትሰበሰቡበት ጊዜ እኔም በመንፈስ ከእናንተ ጋር ስለምሆን፣ በጌታችን በኢየሱስ ስምና በመካከላችሁ በሚገኘው በጌታችን በኢየሱስ ኀይል፣ 5ሥጋው5፥5 ወይም ኀጢአተኛ ተፈጥሮው ወይም አካሉ ጠፍቶ መንፈሱ በጌታ ቀን ትድን ዘንድ፣ እንደዚህ ዐይነቱ ለሰይጣን ይሰጥ።

6መመካታችሁ መልካም አይደለም። ጥቂት እርሾ ብዙውን ሊጥ እንደሚያቦካው አታውቁምን? 7አሁን ያለ እርሾ እንደ ሆናችሁ ሁሉ አዲስ ሊጥ እንድትሆኑ አሮጌውን እርሾ አስወግዱ፤ የፋሲካ በጋችን የሆነው ክርስቶስ ተሠውቷልና። 8ስለዚህ በዓሉን ግፍና ክፋት በሞላበት እርሾ፣ በአሮጌ እርሾ ሳይሆን፣ እርሾ በሌለበት ቂጣ በቅንነትና በእውነት እናክብር።

9ከሴሰኞች ጋር እንዳትተባበሩ በመልእክቴ ጽፌላችሁ ነበር፤ 10እንዲህም ስል በጠቅላላው ከዚህ ዓለም ሴሰኞች ወይም ስግብግቦችና ቀማኞች ወይም ከጣዖት አምላኪዎች ጋር አትተባበሩ ለማለት አይደለም፤ እንደዚያማ ቢሆን ከዚህ ዓለም ጨርሶ መለየት ያስፈልጋችሁ ነበር። 11ነገር ግን አሁን የጻፍሁላችሁ፣ “ወንድም ነኝ” እያለ ከሚሴስን ወይም ከሚስገበገብ ወይም ጣዖትን ከሚያመልክ ወይም ከሚሳደብ ወይም ከሚሰክር ወይም ከሚቀማ ጋር እንዳትተባበሩ ነው፤ ከእንደዚህ ዐይነቱ ሰው ጋር ምግብ እንኳ አትብሉ።

12ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ባሉት ሰዎች ላይ ለመፍረድ እኔን ምን አግብቶኝ? በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ባሉት ሰዎች ላይ እናንተ አትፈርዱምን? 13ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ባሉት ላይ የሚፈርድ ግን እግዚአብሔር ነው፤ እንግዲህ፣ “ክፉውን ሰው ከመካከላችሁ አስወግዱት።”