約翰一書 2 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約翰一書 2:1-29

1我的孩子們,我寫這些話給你們是為了叫你們不要犯罪。如果有人犯了罪,在父那裡我們有一位護慰者,就是那位義者——耶穌基督。 2祂為我們的罪作了贖罪祭,不只是為我們的罪,也是為全人類的罪。

3我們若遵行上帝的命令,就知道自己認識祂。 4若有人說「我認識祂」,卻不遵行祂的命令,這人是說謊的,他心中沒有真理。 5遵行主話語的人是真正全心愛上帝的人,我們藉此知道自己是在主裡面。 6所以,自稱住在主裡面的,就該在生活中效法基督。

新命令

7親愛的弟兄姊妹,我寫給你們的並不是一條新命令,而是你們起初接受的舊命令,這舊命令就是你們已經聽過的真道。 8然而,我寫給你們的也是新命令,在基督和你們身上都顯明是真實的,因為黑暗漸漸過去,真光已經照耀出來。

9若有人說自己在光明中,卻恨他的弟兄姊妹,他就仍然活在黑暗裡。 10愛弟兄姊妹的人活在光明中,沒有什麼可以絆倒他2·10 沒有什麼可以絆倒他」或譯「他也不會絆倒別人」。11恨弟兄姊妹的人活在黑暗中,走在黑暗中,不知何去何從,因為黑暗弄瞎了他的眼睛。

12孩子們,我寫信給你們,因為靠著祂的名,你們的罪已經得到赦免。 13父老們,我寫信給你們,因為你們認識了從太初就存在的那位。年輕人,我寫信給你們,因為你們已經戰勝了那惡者。

14孩子們,我曾寫信給你們,因為你們認識了父。父老們,我曾寫信給你們,因為你們認識了從太初就存在的那位。年輕人,我曾寫信給你們,因為你們剛強,上帝的道常存在你們心裡,並且你們戰勝了那惡者。

15不要愛世界和世上的事,因為人若愛世界,就不會再有愛父的心了。 16凡屬世界的,如肉體的私慾、眼目的私慾和今生的驕傲都不是從父那裡來的,而是從世界來的。 17這世界和其中一切的私慾都要過去,但遵守上帝旨意的人永遠長存。

防備敵基督者

18孩子們,現在是末世了。你們從前聽說敵基督者要來,其實現在許多敵基督者已經出現了,由此可知,現在是末世了。 19這些人是從我們中間出去的,但他們不屬於我們。他們如果屬於我們,就會留在我們當中了。他們的離去表明他們都不屬於我們。

20你們從那位聖者領受了聖靈2·20 聖靈」希臘文指「膏抹」。,所以你們明白真理。 21我寫信給你們不是因為你們不明白真理,而是因為你們明白真理,並且知道真理裡面絕對沒有謊言。 22誰是說謊的呢?不就是那否認耶穌是基督的嗎?那不承認父和子的就是敵基督者。 23凡否認子的,也否認了父;凡承認子的,也承認了父。

24你們務要把起初所聽見的教導謹記在心,這樣,你們必住在子和父裡面。 25主應許給我們的是永生。 26以上的話是針對那些引誘你們離開正道的人寫的。

順從聖靈

27你們既然從主領受了聖靈,聖靈又住在你們心中,就不需要其他人來教導你們,因為聖靈必會在一切事上指引你們。聖靈的教導是真實的,沒有虛假,你們要按聖靈的教導住在主裡面。 28孩子們,你們要住在主裡面。這樣,當主顯現的時候,就是祂再來的時候,我們便能坦然無懼,不會在祂面前羞愧。 29既然你們知道主是公義的,也該知道所有按公義行事的人都是上帝的兒女。

New Amharic Standard Version

1 ዮሐንስ 2:1-29

1ልጆቼ ሆይ፤ ይህን የምጽፍላችሁ ኀጢአት እንዳትሠሩ ነው፤ ነገር ግን ማንም ኀጢአት ቢሠራ፣ በአብ ዘንድ ጠበቃ አለን፤ እርሱም ጻድቁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። 2እርሱም የኀጢአታችን ማስተስረያ ነው፤ ይኸውም2፥2 ኀጢአታችንን አስወግዶ የእግዚአብሔርን ቍጣ ከእኛ የሚያርቅ እርሱ ነው፤ ይኸውም የእኛን ኀጢአት ብቻ ሳይሆን ማለትም ነው። ለዓለም ሁሉ ኀጢአት እንጂ ለእኛ ብቻ አይደለም።

3ትእዛዞቹን ብንፈጽም እርሱን ማወቃችንን በዚህ ርግጠኞች እንሆናለን። 4“እርሱን ዐውቃለሁ” እያለ ትእዛዙን የማይፈጽም ግን ሐሰተኛ ነው፤ እውነትም በእርሱ ውስጥ የለም። 5ነገር ግን ማንም ቃሉን ቢጠብቅ፣ በእውነት የእግዚአብሔር ፍቅር2፥5 ወይም ለእግዚአብሔር ያለው ፍቅር ማለት ነው። በእርሱ ፍጹም ሆኗል። በእርሱ መሆናችንን የምናውቀው በዚህ ነው፤ 6ማንም በእርሱ እኖራለሁ የሚል፣ ኢየሱስ እንደ ተመላለሰ ሊመላለስ ይገባዋል።

7ወዳጆች ሆይ፤ የምጽፍላችሁ፣ ከመጀመሪያ የነበራችሁን የቈየውን ትእዛዝ እንጂ አዲስ ትእዛዝ አይደለም፤ የቈየው ትእዛዝ የሰማችሁት ቃል ነው። 8በሌላ በኩል የምጽፍላችሁ ጨለማው እያለፈና እውነተኛው ብርሃን እየበራ ስለሆነ፣ በእርሱም፣ በእናንተም ዘንድ እውነት የሆነውን አዲስ ትእዛዝ ነው።

9በብርሃን አለሁ የሚል፣ ወንድሙን ግን የሚጠላ አሁንም በጨለማ ውስጥ አለ። 10ወንድሙን የሚወድድ በብርሃን ይኖራል፤ በእርሱም ዘንድ የመሰናከያ ምክንያት የለውም። 11ነገር ግን ወንድሙን የሚጠላ በጨለማ ውስጥ ነው፤ በጨለማ ይመላለሳል፤ ጨለማው ስላሳወረውም የት እንደሚሄድ አያውቅም።

12ልጆች ሆይ፤

ኀጢአታችሁ ስለ ስሙ ተሰርዮላችኋልና፣

እጽፍላችኋለሁ።

13አባቶች ሆይ፤

ከመጀመሪያ ያለውን እርሱን ዐውቃችሁታልና፣ እጽፍላችኋለሁ።

ጐበዛዝት ሆይ፤ ክፉውን አሸንፋችኋልና፣ እጽፍላችኋለሁ።

ልጆች ሆይ፤ አብን ዐውቃችሁታልና፣ እጽፍላችኋለሁ።

14አባቶች ሆይ፤

ከመጀመሪያ ያለውን እርሱን ዐውቃችሁታልና፣

እጽፍላችኋለሁ።

ጐበዛዝት ሆይ፤

ብርቱዎች ስለ ሆናችሁ፣

የእግዚአብሔር ቃል በእናንተ ስለሚኖር፣

ክፉውንም ስላሸነፋችሁ፣

እጽፍላችኋለሁ።

ዓለምን አትውደዱ

15ዓለምን ወይም በዓለም ያለውን ማናቸውንም ነገር አትውደዱ፤ ማንም ዓለምን ቢወድድ የአብ ፍቅር በእርሱ ዘንድ የለም፤ 16ምክንያቱም በዓለም ያለው ሁሉ፦ የሥጋ ምኞት፣ የዐይን አምሮትና የኑሮ ትምክሕት ከዓለም እንጂ ከአብ የሚመጣ አይደለም። 17ዓለምና ምኞቱ ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚፈጽም ግን ለዘላለም ይኖራል።

ከክርስቶስ ተቃዋሚዎች መጠንቀቅ

18ልጆች ሆይ፤ ይህ የመጨረሻው ሰዓት ነው፤ እንደ ሰማችሁትም የክርስቶስ ተቃዋሚ ይመጣል፤ አሁን እንኳ ብዙ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች መጥተዋል፤ የመጨረሻው ሰዓት እንደ ሆነ የምናውቀውም በዚህ ነው።

19ከእኛ መካከል ወጡ፤ ይሁን እንጂ ከእኛ ወገን አልነበሩም፤ ከእኛ ወገን ቢሆኑማ ኖሮ ከእኛ ጋር ጸንተው በኖሩ ነበር። ነገር ግን ሁሉም ከእኛ ወገን እንዳልነበሩ ይታወቅ ዘንድ ከእኛ ተለዩ።

20እናንተ ግን ከእርሱ፣ ከቅዱሱ ቅባት አላችሁና፣ ሁላችሁም እውነትን2፥20 አንዳንድ ቅጆች፣ እናንተ ሁሉንም ነገር ታውቃላችሁ ይላሉ። ታውቃላችሁ። 21እኔ የምጽፍላችሁ እውነትን ስለማታውቁ አይደለም፤ ነገር ግን እውነትን ስለምታውቁትና ከእውነት ምንም ውሸት ስለማይወጣ ነው። 22ክርስቶስ አይደለም ብሎ ኢየሱስን ከሚክድ በቀር ሐሰተኛ ማነው? ይህ አብንና ወልድን የሚክደው የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው። 23ወልድን የሚክድ ሁሉ አብ የለውም፤ ወልድን የሚያምን ሁሉ አብም አለው።

24ከመጀመሪያ የሰማችሁት በእናንተ ውስጥ ይኑር፤ ከመጀመሪያ የሰማችሁት በእናንተ ውስጥ ቢኖር፣ እናንተም በወልድና በአብ ትኖራላችሁ። 25ይህ እርሱ የሰጠን ተስፋ የዘላለም ሕይወት ነው።

26ስለሚያስቷችሁ ሰዎች ይህን ጽፌላችኋለሁ። 27እናንተ ግን ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በውስጣችሁ ይኖራልና ማንም እንዲያስተምራችሁ አያስፈልግም፤ ነገር ግን እውነት እንጂ ሐሰት ያልሆነው የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉም ነገር እንደሚያስተምራችሁ፣ ያም እውነት እንጂ ሐሰት እንዳልሆነ፣ እናንተንም እንዳስተማራችሁ በእርሱ ኑሩ።

የእግዚአብሔር ልጆች

28እንግዲህ ልጆች ሆይ፤ እርሱ ሲገለጥ ድፍረት እንዲኖረን፣ በሚመጣበትም ጊዜ በፊቱ እንዳናፍር በእርሱ ኑሩ።

29እርሱ ጻድቅ መሆኑን ካወቃችሁ፣ ጽድቅን የሚያደርግ ሁሉ ከእርሱ እንደ ተወለደ ታውቃላችሁ።