約伯記 5 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約伯記 5:1-27

1「你只管呼救吧,

誰會回應你呢?

你向哪位聖者求助呢?

2憤恨害死愚昧人,

嫉妒殺死無知者。

3我見愚昧人扎了根,

突然咒詛臨到他家。

4他的兒女毫無安寧,

在城門口受欺壓也無人搭救。

5饑餓的人吞掉他的莊稼,

連荊棘裡的也不放過;

乾渴的人吞盡他的財富。

6苦難並非從土裡長出,

患難並非從地裡生出。

7人生來必遇患難,

正如火花必向上飛。

8「若是我,

就向上帝求助,

向祂陳明苦衷。

9祂行的奇事不可測度,

祂行的神蹟不可勝數。

10祂降下雨水澆灌大地,

賜下甘霖滋潤田園。

11祂提拔卑微的人,

庇護哀痛的人。

12祂挫敗狡猾人的陰謀,

使他們無法得逞。

13祂使智者中了自己的詭計,

使奸徒的計謀迅速落空。

14他們白天遇到黑暗,

午間摸索如在夜晚。

15上帝拯救窮苦人脫離惡人的中傷,

脫離殘暴之徒的轄制,

16好使貧寒之人有盼望,

使不義之徒啞口無言。

17「被上帝責備的人有福了,

不可輕視全能者的管教。

18因為祂打傷,祂也包紮;

祂擊傷,祂也醫治。

19六次遭難,祂都救你;

第七次,災禍也傷不到你。

20饑荒時,祂必救你脫離死亡;

戰爭中,祂必救你脫離刀劍。

21你必免受惡毒的譭謗,

災難來臨也不懼怕。

22你必笑對災殃和饑荒,

毫不懼怕地上的野獸。

23你必與田間的石頭立約,

野獸必與你和平相處。

24你的家必安然無恙,

察看羊圈,一隻不少。

25你必看見子孫昌盛,

後代如遍地的青草。

26你必壽終正寢才歸墳墓,

如同莊稼熟後才被收割。

27看啊,我們已經查驗了,

這一切真實可靠,

你當聆聽、接受。」

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 5:1-27

1“እስቲ ተጣራ፤ የሚመልስልህ አለን?

ከቅዱሳንስ ወደ ማንኛው ዘወር ትላለህ?

2ሞኙን ሰው ብስጭት ይገድለዋል፤

ቂሉንም ቅናት ያጠፋዋል።

3ቂል ሰው ሥር ሰድዶ አየሁት፤

ግን ድንገት ቤቱ ተረገመ።

4ልጆቹ የኑሮ ዋስትና የራቃቸው፤

በፍርድ አደባባይ ጥቃት የደረሰባቸው፣ ታዳጊ የሌላቸው ናቸው።

5ከእሾኽ መካከል እንኳ አውጥቶ፣

ራብተኛ ሰብሉን ይበላበታል፤

ጥማተኛም ሀብቱን ይመኝበታል።

6ችግር ከምድር አይፈልቅም፤

መከራም ከመሬት አይበቅልም።

7ፍንጣሪው ከእሳቱ ላይ ሽቅብ እንደሚወረወር፣

ሰውም ለመከራ ይወለዳል።

8“እኔ ብሆን ኖሮ፣ ወደ እግዚአብሔር በቀረብሁ፣

ጕዳዬንም በፊቱ በገለጽሁለት ነበር።

9እርሱ፣ የማይመረመሩ ድንቅ ነገሮች፣

የማይቈጠሩም ታምራት ያደርጋል።

10ምድሪቱን በዝናብ ያረሰርሳል፤

ሜዳውንም ውሃ ያጠጣል።

11የተዋረዱትን በከፍታ ቦታ ያስቀምጣል፤

ያዘኑትንም ወደ አስተማማኝ ስፍራ ያወጣቸዋል።

12እጃቸው ያሰቡትን እንዳይፈጽም፣

የተንኰለኞችን ዕቅድ ያከሽፋል።

13ጠቢባንን በጥበባቸው ይይዛል፤

የተንኰለኞችንም ሤራ ያጠፋል።

14ቀኑ ጨለማ ይሆንባቸዋል፤

በቀትርም ጊዜ በሌሊት እንዳለ ሰው በዳበሳ ይሄዳሉ።

15ችግረኛውን ከአፋቸው ሰይፍ፣

ከኀይለኛውም እጅ ያድነዋል።

16ስለዚህ ድኻ ተስፋ አለው፤

ዐመፅም አፏን ትዘጋለች።

17“እነሆ፤ እግዚአብሔር የሚገሥጸው ሰው ምስጉን ነው፤

ስለዚህ ሁሉን የሚችለውን5፥17 በዕብራይስጥ ሻዳይ ማለት ሲሆን፣ በዚህ ቍጥርና በኢዮብ መጽሐፍ ውስጥም እንዲሁ ነው። አምላክ ተግሣጽ አትናቅ።

18እርሱ ያቈስላል፤ ይፈውሳል፤

እርሱ ይሰብራል፤ በእጁም ይጠግናል፤

19እርሱ ከስድስት መቅሠፍት ይታደግሃል፤

በሰባተኛውም ጕዳት አያገኝህም።

20በራብ ጊዜ ከሞት፣

በጦርነትም ከሰይፍ ያድንሃል።

21ከምላስ ጅራፍ ትሰወራለህ፤

ጥፋት ሲመጣም አትፈራም።

22በጥፋትና በራብ ላይ ትሥቃለህ፤

የምድርንም አራዊት አትፈራም።

23ከሜዳ ድንጋዮች ጋር ትዋዋላለህና፤

የዱር አራዊትም ከአንተ ጋር ይስማማሉ።

24ድንኳንህ በሚያስተማምን ሁኔታ እንዳለ ታውቃለህ፤

በረትህን ትቃኛለህ፤ አንዳችም አይጐድልብህም።

25ዘሮችህ አያሌ እንደሚሆኑ፣

የምትወልዳቸውም እንደ ሣር እንደሚበዙ ታውቃለህ።

26የእህል ነዶ ጐምርቶ በወቅቱ እንደሚሰበሰብ፣

ዕድሜ ጠግበህ ወደ መቃብር ትሄዳለህ።

27“እነሆ፤ ይህን ሁሉ መርምረናል፤ እውነት ሆኖ አግኝተነዋል፤

ስለዚህ ልብ በል፤ ተቀበለውም።”