約伯記 27 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約伯記 27:1-23

1約伯接著說:

2「我憑不給我公道的永恆上帝,

憑使我靈魂陷入痛苦的全能者起誓,

3只要我一息尚存,

鼻中還有上帝之氣,

4我的嘴唇決不說惡語,

舌頭決不講謊話。

5我決不承認你們有理,

我至死堅信自己無辜。

6我堅守自己的公義,決不放棄,

我有生之年都問心無愧。

7「願我仇敵的下場和惡人一樣,

願我對頭的結局和罪人相同。

8因為不敬虔的人將被剷除,上帝將奪去他的性命。

那時,他還有何指望?

9患難臨到他時,

上帝豈會垂聽他的呼求?

10他豈會以全能者為樂,

時時求告上帝?

11「我要教導你們有關上帝的能力,

我不會隱瞞全能者的作為。

12其實你們也曾親眼目睹,

為何還講這些虛妄之言?

13「以下是上帝給惡人定的結局,

全能者賜給殘暴之徒的歸宿。

14他的兒女再多也難逃殺戮,

他的子孫永遠吃不飽。

15他倖存的後人被瘟疫吞噬,

生還的寡婦也不哀哭。

16儘管他堆積的銀子多如塵沙,

儲存的衣服高若土堆,

17但義人將穿他儲存的衣服,

清白的人將分他堆積的銀子。

18他建的房子像蛾繭,

像守望者搭的草棚。

19他睡前還是富翁,

醒來後財富已空。

20恐懼如洪水般淹沒他,

暴風在夜間把他捲去。

21東風把他颳走,

吹得無影無蹤。

22狂風27·22 狂風」希伯來文指代不清,也可譯作「祂」,指上帝,23節同。毫不留情地擊打他,

他拼命地逃離風的威力。

23狂風向他拍掌,

呼嘯著吹走他。

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 27:1-23

1ኢዮብም እንዲህ ሲል ንግግሩን ቀጠለ፤

2“ፍትሕ የነሣኝ ሕያው እግዚአብሔርን!

ነፍሴንም መራራ ያደረጋት፣ ሁሉን ቻይ አምላክን!

3በውስጤ የሕይወት እስትንፋስ፣

በአፍንጫዬም ውስጥ የእግዚአብሔር መንፈስ እስካለ ድረስ፣

4ከንፈሬ ኀጢአትን አትናገርም፤

አንደበቴም ሽንገላ አይወጣውም።

5እናንተን እንደ ቅኖች መቍጠር፣

የማላደርገው ነገር ነው፤ ጨዋነቴንም እስክሞት ድረስ አልጥልም።

6ጽድቄን አጥብቄ እይዛለሁ፤ አልለቀውምም፤

በዘመኔም ሁሉ ኅሊናዬ አይወቅሠኝም።

7“ጠላቴ እንደ በደለኛ፣

ባላንጣዬም እንደ ክፉ ይሁን።

8እግዚአብሔር ሲያስወግደው፣

ነፍሱንም ሲወስድበት ዐመፀኛ ምን ተስፋ አለው?

9በውኑ መከራ በገጠመው ጊዜ፣

እግዚአብሔር ጩኸቱን ይሰማልን?

10ሁሉን በሚችል አምላክ ደስ ይለዋልን?

ዘወትርስ እግዚአብሔርን ይጠራልን?

11“ስለ እግዚአብሔር ክንድ አስተምራችኋለሁ፤

የሁሉን ቻዩንም አምላክ ዕቅድ አልሸሽግም።

12ሁላችሁ ይህን አይታችኋል፤

ታዲያ፣ ይህ ከንቱ ንግግር ምንድን ነው?

13“እግዚአብሔር ለክፉው የመደበው ዕድል ፈንታ፣

ግፈኛም ሁሉን ከሚችል አምላክ የሚቀበለው ቅርስ ይህ ነው፦

14ልጆቹ የቱንም ያህል ቢበዙም ለሰይፍ ይዳረጋሉ፤

ዘሩም ጠግቦ አያድርም።

15የተረፉለትም በመቅሠፍት ዐልቀው ይቀበራሉ፤

መበለቶቻቸውም አያለቅሱላቸውም።

16ብርን እንደ ዐፈር ቢከምር፣

ልብስንም እንደ ሸክላ ጭቃ ቢያከማች፣

17እርሱ ያከማቸውን ጻድቃን ይለብሱታል፤

ብሩንም ንጹሓን ይከፋፈሉታል።

18የሚሠራው ቤት እንደ ሸረሪት ድር፣

እህል ጠባቂም እንደ ቀለሰው መጠለያ ነው።

19ሀብታም ሆኖ ይተኛል፤ ዘለቄታ ግን የለውም፤

ዐይኑን በገለጠ ጊዜ ሀብቱ ሁሉ በቦታው የለም።

20ድንጋጤ እንደ ጐርፍ ድንገት ያጥለቀልቀዋል፤

ዐውሎ ነፋስም በሌሊት ይዞት ይሄዳል።

21የምሥራቅ ነፋስ ይወስደዋል፤ እርሱም አይገኝም፤

ከስፍራውም ይጠርገዋል።

22ከነፋሱ ብርታት ለማምለጥ ይሮጣል፤

ነገር ግን እየተወረወረ ያለ ርኅራኄ ይደርስበታል፤

23እጁንም እያጨበጨበ ያሾፍበታል፤

በፉጨትም ከስፍራው ያሽቀነጥረዋል።”