約伯記 24 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約伯記 24:1-25

1「全能者為何不定下審判的日期?

為何信靠祂的人要空等一場?

2惡人挪移界石,

搶奪羊群去牧養。

3他們牽走孤兒的驢,

強取寡婦的牛作抵押。

4他們把貧民趕離正路,

地上的窮人被迫東躲西藏。

5貧窮的人如荒漠中的野驢,

殷勤覓食,給兒女糊口。

6他們割田間的草料,

摘惡人剩餘的葡萄。

7他們整夜赤身露體,

沒有被子可以禦寒。

8他們被山雨澆透,

只能在岩石下棲身。

9惡人奪去寡母懷中的孤兒,

強取窮人的孩子作抵押,

10使他們赤身露體地流浪,

餓著肚子扛禾捆。

11他們在惡人的橄欖林中榨油,

口乾舌燥地在酒池踩踏。

12城中傳來垂死之人的呻吟,

受傷者不斷呼救,

上帝卻置之不理。

13「有人與光明為敵,

不認識光明之道,

也不走光明之路。

14兇手黎明起來,

殺害貧苦的人,

夜晚又去做賊。

15姦夫的眼睛盼著黃昏,

心想,『沒人會看見我』,

並把臉蒙起來。

16盜賊夜間挖牆行竊,

日間躲藏起來,

不想認識光明。

17他們以晝作夜,

熟知黑夜的恐怖。

18「惡人如水上的泡沫。

他們的產業遭咒詛,

他們的葡萄園荒蕪。

19陰間吞噬犯罪之人,

如同乾熱吞噬融雪。

20他們的生母忘記他們,

蟲子在他們身上飽餐。

沒有人再記得他們,

惡人像樹木一樣折斷。

21他們惡待不育的婦人,

毫不善待寡婦。

22但上帝用大能擄走權貴,

他們再強大也難保性命。

23上帝讓他們暫享安逸,

但他們逃不過祂的眼睛。

24他們一時得勢,轉瞬消逝;

他們淪為卑賤,像其他人一樣滅亡,

像麥穗一樣被割掉。

25我說的都是實情,誰能否認?

誰能證明我的話是空談?」

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 24:1-25

1“ሁሉን የሚችል አምላክ ለምን የፍርድ ቀን አይወስንም?

እርሱን የሚያውቁትስ ለምን ያን ቀን እንዲያው ይጠባበቃሉ?

2ሰዎች ድንበር ይገፋሉ፤

የሰረቁትን መንጋ ያሰማራሉ።

3የድኻ ዐደጉን አህያ ቀምተው ይሄዳሉ፤

የመበለቲቱንም በሬ በመያዣነት ይወስዳሉ።

4ችግረኛውን ከመንገድ ያስወግዳሉ፤

የምድሪቱም ድኾች ይሸሸጋሉ።

5በምድረ በዳ እንዳሉ የሜዳ አህዮች፣

ድኾች ምግብ ፍለጋ ይራወጣሉ፤

ከበረሓው ምድር ለልጆቻቸው ምግብ ይሻሉ።

6ከሜዳ መኖ ይሰበስባሉ፤

ከክፉዎች የወይን ቦታም ይቃርማሉ።

7ዕራቍታቸውን ያለ ልብስ ያድራሉ፤

በብርድም ጊዜ የሚለብሱት የላቸውም።

8ከተራራ በሚወርድ ዝናብ በስብሰዋል፤

መጠለያ ዐጥተው ቋጥኝ ዐቅፈዋል።

9አባት የሌለው ልጅ ከዕቅፍ ተነጥቋል፤

የድኻውም ልጅ በዕዳ ተይዟል።

10ዕራቍታቸውን ያለ ልብስ ይሄዳሉ፤

ነዶ ይሸከማሉ፤ ግን ይራባሉ።

11በየተረተሩ24፥11 ወይም ከወፍጮዎች መካከል የወይራ ዘይት ማለት ነው፤ ሆኖም የዚህ ቃል የዕብራይስጡ ትርጕም በትክክል አይታወቅም። የወይራ ዘይት ያወጣሉ፤

ወይን እየጠመቁ፣ ራሳቸው ግን ይጠማሉ፤

12የሟቾች ጣር ጩኸት ከከተማዋ ይሰማል፤

የቈሰሉት ሰዎች ነፍስ ለርዳታ ይጮኻል፤

እግዚአብሔር ግን ተጠያቂዎቹን ዝም ብሏል።

13“በብርሃን ላይ የሚያምፁ፣

ጐዳናውን የማያውቁ፣

በመንገዱም የማይጸኑ አሉ።

14ቀኑ ሲመሽ፣ ነፍሰ ገዳይ ይነሣል፤

ድኾችንና ችግረኞችን ይገድላል፤

በሌሊትም እንደ ሌባ ያደባል፤

15አመንዝራ በዐይኑ ድንግዝግዝታን ይጠባበቃል፤

‘ማንም አያየኝም’ ብሎ ያስባል፤

ፊቱንም ይሸፍናል።

16በጨለማ፣ ቤት ሰርስረው ይገባሉ፤

በቀን ግን ይሸሸጋሉ፤

ብርሃንንም አይፈልጉም።

17ድቅድቅ ጨለማ ለሁላቸው እንደ ንጋት24፥17 ወይም ለእነርሱ ንጋት እንደ ሞት ጥላ ነው ነው፤

አሸባሪውን ጨለማ24፥17 ወይም ከሞት ጥላ ማለት ነው። ይወዳጃሉ።

18“ይሁን እንጂ፣ በውሃ ላይ የሚኵረፈረፍ ዐረፋ ናቸው፤

የወይን ቦታው ሰው የማይደርስበት፣

ርስታቸው ርጉም ነው።

19ድርቅና ሙቀት የቀለጠውን በረዶ ከቦታው እንደሚያስወግድ፣

ሲኦልም24፥19 አንዳንድ ቅጆች፣ መቃብር ይሉታል ኀጢአተኞችን ትነጥቃለች።

20የተሸከመቻቸው ማሕፀን ትረሳቸዋለች፤

ትል ይቦጠቡጣቸዋል፤

ክፉዎች እንደ ዛፍ ይሰበራሉ፤

የሚያስታውሳቸውም የለም።

21የማትወልደውን መካኒቱን ይቦጠቡጣሉ፤

ለመበለቲቱም አይራሩም።

22ነገር ግን እግዚአብሔር ብርቱዎችን በኀይሉ ጐትቶ ይጥላል፤

ቢደላደሉም የሕይወት ዋስትና የላቸውም።

23ያለ ሥጋት እንዲኖሩ ትቷቸው ይሆናል፤

ዐይኖቹ ግን በመንገዳቸው ላይ ናቸው።

24ለጥቂት ጊዜ ከፍ ከፍ ይላሉ፤ ሆኖም ይጠፋሉ፤

ዝቅ ዝቅ ብለው፤ እንደ ሌሎቹ ይከማቻሉ።

እንደ እህል ራስም ይታጨዳሉ።

25“ይህ እንዲህ ካልሆነማ፣ የሚያስተባብለኝ ማን ነው?

ቃሌን ከንቱ የሚያደርገውስ ማን ነው?”