約伯記 20 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約伯記 20:1-29

瑣法再度發言

1拿瑪瑣法回答說:

2「我感到煩躁不安,

心中有話不吐不快。

3我聽見你侮辱我的斥責,

我的理智催促我回答。

4難道你不知道,從古至今,

自從世上有人以來,

5惡人得勢不會長久,

不信上帝者的快樂轉瞬即逝?

6雖然他傲氣沖天,

把頭挺到雲端,

7終必如自己的糞便永遠消亡,

見過他的人都不知他在何處。

8他如夢消逝,蹤影杳然;

如夜間的異象,飛逝而去。

9見過他的人不會再見到他,

他將從家鄉消失無蹤。

10他的兒女要向窮人乞憐,

他要親手償還不義之財。

11他的筋骨依然強健,

卻要隨他葬入塵土。

12「他以邪惡為甘飴,

將其藏在舌下,

13含在口中,

慢慢品味。

14這食物在腹中變酸,

變成了蛇的毒液。

15他要吐出所吞下的財富,

上帝要倒空他腹中之物。

16他吸吮蛇的毒液,

被蛇的舌頭害死。

17他無法享用流淌不盡的奶與蜜。

18他留不住勞碌的成果,

無法享用所賺的財富。

19他欺壓、漠視窮人,

強佔別人的房屋。

20他貪慾無度,

不放過任何喜愛之物。

21他吞掉一切所有,

他的福樂不能長久。

22他在富足時將陷入困境,

各種災禍將接踵而至。

23上帝的怒火如雨降在他身上,

填滿他的肚腹。

24他躲過了鐵刃,

卻被銅箭射穿。

25利箭穿透他的後背,

閃亮的箭頭刺破他的膽囊,

恐怖籠罩著他。

26他的財寶消失在幽冥中,

天火20·26 天火」希伯來文是「非人手點燃的火」。要吞噬他,

焚毀他帳篷中殘留的一切。

27天要揭露他的罪惡,

地要站出來指控他。

28在上帝發烈怒的日子,

洪流將席捲他的家產。

29這便是上帝為惡人定下的結局,

為他們預備的歸宿。」

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 20:1-29

ሶፋር

1ናዕማታዊውም ሶፋር እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“እጅግ ታውኬአለሁና፣

ሐሳቤ መልስ እንድሰጥ ይጐተጕተኛል።

3የሚያቃልለኝን ንግግር ሰምቼአለሁ፤

መልስም እሰጥ ዘንድ መንፈሴ ገፋፋኝ።

4“ሰው20፥4 ወይም አዳም ማለት ነው። በምድር ላይ ከተቀመጠ ጊዜ ጀምሮ፣

ከጥንቱ እንዴት እንደ ነበረ ታውቃለህን?

5የኀጢአተኞች መፈንጨት ለዐጭር ጊዜ፣

የክፉዎችም ደስታ ለቅጽበት መሆኑን አታውቅምን?

6እስከ ሰማይ ከፍ ከፍ ቢልም፣

ዐናቱም ደመናትን ቢነካ፣

7እንደ ኵበት ለዘላለም ይጠፋል፤

ቀድሞ ያዩትም፣ ‘የት ገባ?’ ይላሉ።

8እንደ ሕልም በርሮ ይጠፋል፤ አይገኝምም፤

እንደ ሌሊትም ራእይ በቅጽበት ያልፋል።

9ቀድሞ ያየው ዐይን ዳግመኛ አያየውም፤

የነበረበትም ቦታ ከእንግዲህ አይመለከተውም።

10ልጆቹ ለድኾች ካሳ መክፈል አለባቸው፤

እጆቹም ሀብቱን መልሰው መስጠት ይገባቸዋል።

11ዐጥንቱን የሞላው የወጣትነት ብርታት፣

ከእርሱ ጋር በዐፈር ውስጥ ይተኛል።

12“ክፋት በአፉ ውስጥ ቢጣፍጥ፣

ከምላሱም በታች ቢደብቀው፣

13አውጥቶ ለመጣል እየሳሳ፣

በአፉ ውስጥ ቢያቈየው፣

14ምግቡ በሆዱ ውስጥ ይመርራል፤

በውስጡም እንደ እባብ መርዝ ይሆናል።

15የዋጠውን ሀብት ይተፋል፤

እግዚአብሔርም መልሶ ከሆዱ ያወጣዋል።

16የእባብ መርዝ ይጠባል፤

የእፉኝትም ምላስ ይገድለዋል።

17ማርና ቅቤ በሚያፈስሱ ጅረቶች፣

በወንዞችም አይደሰትም።

18የለፋበትን ሳይበላው ይመልሳል፤

ከንግዱም ባገኘው ትርፍ አይደሰትም፤

19ድኾችን በመጨቈን ባዶ

አስቀርቷቸዋልና፣ ያልሠራውንም ቤት ነጥቋል።

20“ክፉ ምኞቱ ዕረፍት አይሰጠውም

ሀብቱም ሊያድነው አይችልም።

21ያለውን አሟጥጦ ስለሚበላ፣

ዘላቂ ብልጽግና አይኖረውም።

22በተድላ መካከል እያለ ጕስቍልና ይመጣበታል፤

በከባድ መከራም ይዋጣል።

23ሆዱን በሞላ ጊዜ፣

እግዚአብሔር የሚነድድ ቍጣውን ይሰድበታል፤

መዓቱንም ያወርድበታል።

24ከብረት መሣሪያ ቢሸሽም፣

የናስ ቀስት ይወጋዋል።

25ቀስቱን ከጀርባው፣

የሚያብለጨልጨውንም ጫፍ ከጕበቱ ይመዝዛል፤

ፍርሀትም ይይዘዋል፤

26ሀብቱ ለድቅድቅ ጨለማ ተዳርጓል፤

ሰው ባላራገበው እሳት ይበላል፤

በድንኳኑም ውስጥ የተረፈውን ይልሳል።

27ሰማያት ኀጢአቱን ይገልጡበታል፤

ምድርም ትነሣበታለች፤

28በእግዚአብሔር የቍጣ ቀን ቤቱን ጐርፍ፣

መኖሪያውንም ወራጅ ውሃ20፥28 ወይም በቤቱ ውስጥ ያለውን ንብረት ወራጅ ውሃ ይወስድበታል ማለት ነው። ይወስድበታል።

29እግዚአብሔር ለኀጢአተኞች የወሰነው ዕድል ፈንታ፣

ከአምላክም ዘንድ የተመደበላቸው ቋሚ ቅርስ ይህ ነው።”