約伯記 15 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約伯記 15:1-35

以利法再次發言

1提幔以利法回答說:

2「智者豈會用空談作答,

滿腹東風?

3申辯時豈會講無用的話,

說無益之言?

4你摒棄對上帝的敬畏,

拒絕向祂禱告。

5你的罪指示你開口,

使你說出詭詐之言。

6並非我定你的罪,

定你罪的是你的口,

指控你的是你的嘴唇。

7你豈是第一個出生的人?

你豈在群山之前被造?

8你豈聽過上帝的密旨?

你豈獨攬智慧?

9有何事你知而我們不知,

你懂而我們不懂?

10我們這裡有白髮老人,

比你父親還年長。

11上帝用溫柔的話安慰你,

難道你還嫌不夠嗎?

12你為何失去理智,

為何雙眼冒火,

13以致你向上帝發怒,

口出惡言?

14人算什麼,怎能純潔?

婦人所生的算什麼,怎能公義?

15連上帝的聖者都無法令祂信任,

連諸天在祂的眼中都不潔淨,

16更何況可憎敗壞、

嗜惡如喝水的世人?

17「讓我告訴你,你好好聽著。

我要把所見的陳明——

18那是智者的教導,

是他們未曾隱瞞的祖訓。

19這片土地只賜給了他們,

沒有外人在他們中間出入。

20惡人一生受折磨,

殘暴之徒終身受苦。

21他耳邊響著恐怖的聲音,

他安逸時遭強盜襲擊。

22他不指望能逃脫黑暗,

他註定要喪身刀下。

23他到處流浪,尋找食物,

他知道黑暗之日快要來臨。

24患難和痛苦使他害怕,

像君王上陣一樣震懾他。

25因為他揮拳對抗上帝,

藐視全能者,

26拿著堅盾傲慢地挑戰祂。

27他滿臉肥肉,

腰間堆滿脂肪。

28他住的城邑必傾覆,

他的房屋必成為一堆瓦礫,

無人居住。

29他不再富足,

家財不能久留,

地產無法加增。

30他無法逃脫黑暗,

火焰要燒焦他的嫩枝,

上帝口中的氣要毀滅他。

31他不可自欺,信靠虛空,

因為虛空必成為他的回報。

32在他離世以前,虛空必臨到他,

他的枝子再不會青綠。

33他必像一棵葡萄樹,

葡萄未熟已掉落;

又像一棵橄欖樹,

花剛開便凋零。

34不信上帝之輩必不生育,

受賄者的帳篷必被火燒。

35他們心懷不軌,生出罪惡,

他們滿腹詭詐。」

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 15:1-35

ኤልፋዝ

1ቴማናዊው ኤልፋዝ እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“ጠቢብ ሰው በከንቱ ንግግር መልስ ይሰጣልን?

ወይስ በምሥራቅ ነፋስ ሆዱን ይሞላል?

3በማይረባ ቃል፣

ፍሬ ቢስ በሆነም ንግግር ይከራከራልን?

4አንተ ግን እግዚአብሔርን መፍራት ታጣጥላለህ፤

አምልኮተ እግዚአብሔርን ትከለክላለህ።

5ኀጢአትህ አፍህን ታስተምረዋለች፤

የተንኰለኞችንም አነጋገር መርጠህ ትይዛለህ።

6የሚፈርድብህ አንደበትህ እንጂ እኔ አይደለሁም፣

የሚመሰክርብህም እኔ ሳልሆን የገዛ ከንፈርህ ነው።

7“ለመሆኑ ከሰው ሁሉ ቀድመህ የተወለድህ አንተ ነህን?

ወይስ ከኰረብቶች በፊት ተገኝተሃል?

8በእግዚአብሔር የመማክርት ጉባኤ ላይ ነበርህን?

ጥበብስ የተሰጠው ለአንተ ብቻ ነው?

9እኛ የማናውቀው አንተ ግን የምታውቀው ምን ነገር አለ?

እኛስ የሌለን አንተ ያለህ ማስተዋል የቱ ነው?

10በዕድሜ ከአባትህ የሚበልጡ፣

የሸበቱ ሽማግሌዎች ከእኛ ጋር አሉ።

11የእግዚአብሔር ማጽናናት፣

በርጋታ የተነገረህ ቃል አነሰህን?

12ልብህ ለምን ይሸፍታል?

ዐይንህንስ ምን ያጕረጠርጠዋል?

13በእግዚአብሔር ላይ እንድትቈጣ፣

እንደዚህ ያለ ቃል ከአፍህ እንዲወጣ ያደረገህ ምንድን ነው?

14“ንጹሕ ይሆን ዘንድ ሰው ምንድን ነው?

ጻድቅስ ይሆን ዘንድ፣ ከሴት የተወለደ ምንድን ነው?

15እነሆ፤ እግዚአብሔር በቅዱሳኑ እንኳ አይታመንም፤

ሰማያትም በእርሱ ፊት ንጹሓን አይደሉም።

16ታዲያ፣ ክፋትን እንደ ውሃ የሚጠጣ፣

አስጸያፊና ርኩስ ሰውማ እንዴት ይታመን!

17“አድምጠኝ፤ በግልጽ አስረዳሃለሁ፤

ያየሁትንም እነግርሃለሁ፤

18ጠቢባን ከአባቶቻቸው የተቀበሉትን፤

ሳይሸሽጉ የተናገሩትን አስረዳሃለሁ፤

19ምድሪቱ ለአባቶቻቸው ተሰጠች፤

በመካከላቸውም ባዕድ አልተቀመጠም፤

20ክፉ ሰው ዕድሜውን ሙሉ፣

ጨካኙም በተመደበለት ዘመን ሁሉ ይሠቃያል።

21የሚያስደነግጥ ድምፅ በጆሮው ላይ ይጮኻል፤

በሰላም ጊዜ ቀማኞች አደጋ ያደርሱበታል።

22ከጨለማ ወጥቶ ማምለጥ ይፈራል፤

ለሰይፍም የተመደበ ነው።

23የአሞራ እራት15፥23 ወይም ለአሞራ እራት ለመፈለግ ለመሆን ይቅበዘበዛል፤

የጨለማ ቀን መቅረቡን ያውቃል።

24ጭንቀትና ሐዘን ያስፈራሩታል፤

ለማጥቃት እንደ ተዘጋጀ ንጉሥም ያይሉበታል፤

25እጁን በእግዚአብሔር ላይ አንሥቷልና፤

ሁሉን የሚችለውን አምላክም ደፍሯል፤

26ወፍራምና ጠንካራ ጋሻ አንግቦ፣

ሊቋቋመው ወጥቷል።

27“ፊቱ በስብ ቢሸፈን፣

ሽንጡ በሥጋ ቢደነድንም፣

28መኖሪያው በፈራረሱ ከተሞች፣

የፍርስራሽ ክምር ለመሆን በተቃረቡ፣

ሰው በማይኖርባቸው ወና ቤቶች ውስጥ ይሆናል።

29ከእንግዲህ ባለጠጋ አይሆንም፤ ሀብቱም አይቈይም፤

ይዞታውም በምድር ላይ አይሰፋም።

30ከጨለማ አያመልጥም፤

ቅርንጫፎቹን ነበልባል ያደርቃቸዋል፤

በእግዚአብሔርም እስትንፋስ ይወሰዳል።

31በአጸፋው አንዳች አያገኝምና፤

ከንቱን ነገር በመታመን ራሱን አያታልል።

32ጊዜው ሳይደርስ ይጠወልጋል፤

ቅርንጫፉም አይለመልምም።

33ፍሬው በጮርቃነት እንደ ተለቀመበት የወይን ተክል፣

አበባውም እንደ ረገፈበት የወይራ ዛፍ ይሆናል።

34የዐመፀኞች ጉባኤ ትመክናለች፤

የጉቦ ሱሰኞችም ድንኳን በእሳት ትበላለች።

35መከራን ይፀንሳሉ፤ ክፋትንም ይወልዳሉ፤

በሆዳቸውም ተንኰል ይጠነስሳሉ።”