箴言 8 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

箴言 8:1-36

智慧的呼喚

1智慧不是在呼喚嗎?

悟性不是在呐喊嗎?

2她在路邊高處站立,

她在十字街頭停留,

3在城門旁,在入口處大喊:

4「世人啊,我呼喚你們,

我向全人類大聲呼籲。

5愚昧人啊,要學會謹慎!

愚頑人啊,要慎思明辨!

6你們聽啊,我要說美好的話,

開口談論正直的事。

7我的口傳揚真理,

我的嘴憎恨邪惡。

8我口中的言語公正,

沒有一句錯謬的話。

9我的話,智者明白,哲士認同。

10要接受我的教誨,而非白銀;

要選擇知識,而非黃金。

11因為智慧比寶石更珍貴,

一切美物都不能與之相比。

12「我智慧與謹慎同住,

我擁有知識和明辨力。

13敬畏耶和華就當憎恨邪惡,

我憎恨驕傲、狂妄、惡道和謊言。

14我有謀略和真知,

又有悟性和能力。

15君王靠我安邦定國,

首領藉我秉公行義,

16王公大臣靠我治理天下,

官宦貴胄憑我公正斷案。

17愛我的,我也愛他;

懇切尋求我的,必能尋見。

18富貴和尊榮在我,

恆久的產業和公義也在我。

19我的果實勝過純金,

我的出產勝過純銀。

20我在公義的道上奔走,

在公平的路上前行。

21我要賜財富給愛我的人,

使他們的庫房充盈。

22「在耶和華造物的起頭,

在太初萬物被造以前,

就已經有我。

23從亙古,從太初,

大地還沒有形成以前,

我已經被立。

24沒有深淵,

沒有湧流的水泉以前,

我已經誕生。

25大山未曾奠定,

小丘未曾形成,

我已經出生。

26那時耶和華還沒有造大地和原野,

還沒有造一粒塵土。

27祂鋪設諸天的時候,我已在場。

祂在深淵上畫出地平線,

28上使穹蒼堅固,

下使深淵的泉源安穩,

29設定滄海的界限,

使海水不得越過祂定的範圍,

為大地奠定根基的時候,

30我就在祂身旁,

做祂的工程師,

天天成為祂的喜樂,

終日在祂面前歡悅,

31因祂所造的人世而歡悅,

因祂所造的世人而喜樂。

32「孩子們啊,你們要聽從我,

持守我道路的人有福了。

33要聽從教誨,不可輕忽,

要做智者。

34人若聽從我、天天在我門口仰望、

時時在我門邊等候,就有福了。

35因為找到我的,便找到了生命,

他必蒙耶和華的恩惠。

36沒找到我就是害自己;

憎恨我就是喜愛死亡。」

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 8:1-36

የጥበብ ጥሪ

1ጥበብ ጮኻ አትጣራምን?

ማስተዋልስ ድምፅዋን ከፍ አድርጋ አታሰማምን?

2በመንገድ አጠገብ ባሉ ኰረብቶች፣

መንገዶቹ በሚገናኙበትም ላይ ትቆማለች፤

3ወደ ከተማዪቱ በሚያስገቡት በሮች አጠገብ፣

በመግቢያዎቹ ላይ፣ ድምፅዋን ከፍ አድርጋ እንዲህ ስትል ትጮኻለች፤

4“ሰዎች ሆይ፤ የምጠራው እኮ እናንተን ነው፤

ለሰው ልጆች ሁሉ ድምፄን ከፍ አደርጋለሁ።

5እናንተ ብስለት የጐደላችሁ፤ ጠንቃቃነትን ገንዘብ አድርጉ፤

እናንተ ተላሎች፤ ማስተዋልን አትርፉ።

6የምናገረው ጠቃሚ ነገር ስላለኝ አድምጡኝ፤

ቀና ነገር ለመናገር ከንፈሮቼን እከፍታለሁ።

7አንደበቴ እውነትን ይናገራል፤

ከንፈሮቼ ክፋትን ይጸየፋሉና።

8ከአንደበቴ የሚወጡት ቃሎች ሁሉ ጽድቅ ናቸው፤

አንዳቸውም ጠማማና ግራ የሚያጋቡ አይደሉም።

9በጥልቅ ለሚያስተውሉ ሁሉም ቀና ናቸው፤

ዕውቀት ላላቸውም ስሕተት የለባቸውም።

10ከብር ይልቅ ምክሬን፣

ከንጹሕ ወርቅ ይልቅ ዕውቀትን ምረጡ፤

11ጥበብ ከቀይ ዕንይበልጥ ውድ ናትና፤

ከምትመኙት ነገር ሁሉ አንዳች የሚስተካከላት የለም።

12“እኔ ጥበብ ከማስተዋል ጋር አብሬ እኖራለሁ፤

ዕውቀትና ልባምነት ገንዘቦቼ ናቸው።

13እግዚአብሔርን መፍራት ክፋትን መጥላት ነው፤

እኔም ትዕቢትንና እብሪትን፣

ክፉ ጠባይንና ጠማማ ንግግርን እጠላለሁ።

14ምክርና ትክክለኛ ፍርድ የእኔ ናቸው፤

ማስተዋል አለኝ፤ ብርታት አለኝ።

15ነገሥታት በእኔ ይነግሣሉ፤

ገዦችም ትክክል የሆነውን ሕግ ይደነግጋሉ፤

16መሳፍንት በእኔ ይገዛሉ፤

በምድር ላይ የሚገዙ መኳንንትም ሁሉ በእኔ ያስተዳድራሉ።8፥16 አያሌ የዕብራይስጥ ቅጆችና የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም፣ ብዙ የዕብራይስጥ ቅጆች በምድር ላይ በጽድቅ የሚገዙ ይላሉ።

17የሚወድዱኝን እወድዳቸዋለሁ፤

ተግተው የሚሹኝም ያገኙኛል።

18ሀብትና ክብር፣

ዘላቂ ብልጽግናና ስኬት በእኔ ዘንድ አሉ።

19ፍሬዬ ከንጹሕ ወርቅ ይበልጣል፤

ስጦታዬም ከነጠረ ብር።

20እኔ በጽድቅ መንገድ እሄዳለሁ፤

በፍትሕም ጐዳና እጓዛለሁ፤

21ለሚወድዱኝ ብልጽግና እሰጣለሁ፤

ግምጃ ቤታቸውንም እሞላለሁ።

22እግዚአብሔር ከቀድሞ ሥራዎቹ በፊት፣

የተግባሮቹ8፥22 ወይም የመንገዱ፣ የግዛቱ መጀመሪያ አድርጎ አመጣኝ፤8፥22 ወይም እግዚአብሔር በሥራው መጀመሪያ ያዘኝ ወይም እግዚአብሔር በሥራው መጀመሪያ አመጣኝ

23ዓለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ፣

ከጥንት ከዘላለም ተሾምሁ።8፥23 ወይም ተሠራ?

24ከውቅያኖሶች በፊት፣

የውሃ ምንጮች ከመፍለቃቸው በፊት ተወለድሁ፤

25ተራሮች ገና ሳይመሠረቱ፣

ከኰረብቶችም በፊት ተወለድሁ፤

26ምድርን ወይም ሜዳዎቿን፣

ወይም ምንም ዐይነት የዓለም ትቢያን ከመፍጠሩ በፊት እኔ ተወለድሁ።

27ሰማያትን በዘረጋ ጊዜ፣

በውቅያኖስ ላይ የአድማስ ምልክት ባደረገ ጊዜ እኔ እዚያ ነበርሁ፤

28ደመናትን በላይ ባጸና ጊዜ፣

የውቅያኖስን ምንጮች በመሠረተ ጊዜ፣

29ለባሕር ድንበርን በከለለ ጊዜ፣

ውሆችም የእርሱን ትእዛዝ እንዳያልፉ፣

የምድርንም መሠረቶች ወሰን ባበጀ ጊዜ፣

30በዚያን ጊዜ ከጐኑ ዋና ባለሙያ ነበርሁ።

ሁልጊዜ በፊቱ ሐሤት እያደረግሁ፣

ዕለት ተዕለት በደስታ እሞላ ነበር፤

31የእርሱ በሆነው መላው ዓለም ሐሤት እያደረግሁ፣

በሰው ልጆች ደስ እሰኝ ነበር።

32“እንግዲህ፣ ልጆቼ ሆይ፤ አድምጡኝ፤

መንገዴን የሚጠብቁ ቡሩካን ናቸው።

33ምክሬን አድምጡ፤ ጥበበኞች ሁኑ፤

ቸልም አትበሉት።

34በየዕለቱ ደጃፌ ላይ የሚጠብቅ፣

በበራፌ ላይ የሚጠባበቅ፣

የሚያዳምጠኝ ሰው ቡሩክ ነው።

35የሚያገኘኝ ሁሉ ሕይወትን ያገኛልና፤

ከእግዚአብሔርም ዘንድ ሞገስን ይቀበላል።

36የሚያጣኝ ሁሉ ግን ራሱ ይጐዳል፤

የሚጠሉኝም ሁሉ ሞትን ይወድዳሉ።”