箴言 30 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

箴言 30:1-33

亞古珥的箴言

1以下是雅基的兒子亞古珥的箴言。

這人說:上帝啊,我很疲倦;

上帝啊,我很疲倦,精疲力盡。30·1 希伯來文或譯「這人對以鐵說,對以鐵和烏甲說:」

2我比眾人都愚蠢,

不具備人的悟性。

3我從未學到智慧,

也不認識至聖者。

4誰升上高天又降下來?

誰將風聚在掌中?

誰將眾水裹在衣服裡?

誰定了地的邊界?

祂叫什麼名字?

祂兒子叫什麼名字?

你知道嗎?

5上帝的話句句千真萬確,

祂作投靠祂之人的盾牌。

6你不可對祂的話有所添加,

免得祂責備你,

揭穿你的虛謊。

7上帝啊,我向你求兩件事,

求你在我未死以前賜給我。

8求你使虛偽和謊言遠離我,

求你讓我不貧窮也不富足,

賜給我需用的飲食,

9免得我因為飽足就不認你,

說:「耶和華是誰呢?」

又恐怕我因窮困而偷竊,

以致辱沒我上帝的名。

10別向主人譭謗他的僕人,

免得你受咒詛、擔當罪責。

11有一種30·11 」希伯來文是「世代」,11-14節也相同。人咒詛父親,

不為母親祝福。

12有一種人自以為純潔,

卻沒有洗掉自己的污穢。

13有一種人趾高氣揚,

目空一切。

14有一種人牙如劍,

齒如刀,

要吞吃世間的困苦人和貧窮人。

15水蛭有兩個女兒,

她們不停地叫:「給我!給我!」

三樣東西從不知足,

永不言「夠」的共有四樣:

16陰間、不孕的婦人、

乾旱的土地和火焰。

17嘲笑父親、藐視母親教誨的,

眼睛必被谷中的烏鴉啄出,

被禿鷹吃掉。

18我測不透的妙事有三樣,

我不明白的事共有四樣:

19鷹在空中飛翔之道,

蛇在石上爬行之道,

船在海中航行之道,

男女相愛之道。

20淫婦的道是這樣:

她吃完就擦擦嘴,

說,「我沒有做壞事。」

21使大地震動的事有三樣,

大地無法承受的事共有四樣:

22奴僕做王,

愚人吃飽,

23醜惡女子出嫁,

婢女取代主母。

24地上有四種動物,

身體雖小卻極其聰明:

25螞蟻力量雖小,

卻在夏天儲備糧食;

26石獾雖不強壯,

卻在岩石中築巢穴;

27蝗蟲雖無君王,

卻整齊地列隊前進;

28壁虎雖易捕捉,

卻居住在王宮大內。

29步履威武的有三樣,

走路雄壯的共有四樣:

30威震百獸、從不畏縮的獅子,

31昂首闊步的雄雞,

公山羊和率領軍隊的君王。

32你若行事愚昧、

妄自尊大或圖謀不軌,

就當用手掩口。

33激起憤怒會引起爭端,

正如攪牛奶會攪出奶油,

擰鼻子會擰出血。

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 30:1-33

አጉር የተናገራቸው ምሳሌዎች

1የያቄ ልጅ የአጉር ቃል ይህ ነው፤30፥1 ወይም የማሳው ያቄ

ይህ ሰው ለኢቲኤል፣

ለኢቲኤልና ለኡካል ተናገረ፤30፥1 የማስሬቲክ ጽሑፍ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የዕብራይስጡ ግን ተናገረ፤ አቤቱ እግዚአብሔር፤ እኔ ደክሜአለሁ፣ ነገር ግን እጸናለሁ ይላል።

2“እኔ ከሰው ሁሉ ይልቅ ጅል ነኝ፤

ሰው ያለው ማስተዋል የለኝም።

3ጥበብን አልተማርሁም፤

ስለ ቅዱሱም ዕውቀት የለኝም።

4ወደ ሰማይ የወጣ፣ የወረደስ ማነው?

ነፋስን በእጁ ሰብስቦ የያዘ ማነው?

ውሆችንስ በመጐናጸፊያው የጠቀለለ ማነው?

የምድርን ዳርቻዎች ሁሉ የወሰነ ማነው?

ስሙ ማን ነው? የልጁስ ስም ማን ይባላል?

የምታውቅ ከሆነ እስቲ ንገረኝ!

5“የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ እንከን የለበትም፤

እርሱ ለሚታመኑበት ሁሉ ጋሻቸው ነው።

6በእርሱ ቃል ላይ አንዳች አትጨምር፤

አለዚያ ይዘልፍሃል፤ ሐሰተኛም ያደርግሃል።

7እግዚአብሔር ሆይ፤ ሁለት ነገር እለምንሃለሁ፤

እነዚህንም ከመሞቴ በፊት አትከልክለኝ፤

8ሐሰትንና ሐሰት መናገርን ከእኔ አርቅልኝ፤

ድኽነትንም ሆነ ብልጽግናን አትስጠኝ፤

ብቻ የዕለት እንጀራዬን ስጠኝ።

9አለዚያ ግን ያለ ልክ እጠግብና እክድሃለሁ፤

እግዚአብሔር ማን ነው?’ እላለሁ፤

ወይም ድኻ እሆንና እሰርቃለሁ፤

የአምላኬንም ስም አሰድባለሁ።

10“አገልጋይን በጌታው ፊት በክፉ አታንሣው፤

አለዚያ ይረግምህና ጕዳት ያገኝሃል።

11“አባቱን የሚረግም፣

እናቱን የማይባርክ ትውልድ አለ፤

12ራሳቸውን ንጹሓን አድርገው የሚቈጥሩ፣

ሆኖም ከርኩሰታቸው ያልነጹ አሉ፤

13ዐይናቸው ትዕቢተኛ የሆነ፣ አስተያያቸው ንቀት የሞላበት፣

14ድኾችን ከምድር፣

ችግረኞችንም ከሰው ዘር መካከል ለማጥፋት፣

ጥርሳቸው ሰይፍ የሆነ፣

መንጋጋቸውም ካራ የሆነ አሉ።

15“አልቅት ሁለት ሴት ልጆች አሉት፤

‘ስጡን! ስጡን!’ እያሉ ይጮኻሉ፤

“ፈጽሞ የማይጠግቡ ሦስት ነገሮች አሉ፤

‘በቃኝን’ ከቶ የማያውቁ አራት ናቸው፤

16እነርሱም መቃብር፣30፥16 ዕብራይስጡ ሲኦል ይላል። መካን ማሕፀን፣

ውሃ ጠጥታ የማትረካ ምድር፣

‘በቃኝ’ የማይል እሳት ናቸው።

17“በአባት ላይ የምታፌዝ ዐይን፣

የእናትንም ትእዛዝ የምትንቅ፣

የሸለቆ ቍራዎች ይጐጠጕጧታል፤

ጆፌ አሞሮችም ይበሏታል።

18“እጅግ የሚያስደንቁኝ ሦስት ነገሮች አሉ፤

የማላስተውላቸውም አራት ናቸው፤

19የንስር መንገድ በሰማይ፣

የእባብ መንገድ በቋጥኝ፣

የመርከብ መንገድ በባሕር፣

የሰውም መንገድ ከሴት ልጅ ጋር ናቸው።

20“የአመንዝራዪቱ መንገድ ይህ ነው፤

በልታ አፏን በማበስ፣

‘ምንም የሠራሁት ጥፋት የለም’ ትላለች።

21“ምድር በሦስት ነገር ትናወጣለች፤

እንዲያውም መሸከም የማትችላቸው አራት ነገሮች ናቸው፤

22ባሪያ ሲነግሥ፣

ሰነፍ እንጀራ ሲጠግብ፣

23የተጠላች ሴት ባል ስታገባ፣

ሴት ባሪያ በእመቤቷ እግር ስትተካ።

24“በምድር ላይ አራት ነገሮች ትንንሽ ናቸው፤

ሆኖም እጅግ ጠቢባን ናቸው፤

25ጕንዳኖች ደካማ ፍጡራን ናቸው፤

ሆኖም ምግባቸውን በበጋ ያከማቻሉ።

26ሽኮኮዎች ዐቅመ ደካማ ናቸው፤

ሆኖም መኖሪያቸውን በቋጥኞች መካከል ይሠራሉ፤

27አንበጦች ንጉሥ የላቸውም፤

ሆኖም ቅደም ተከተል ይዘው ይጓዛሉ፤

28እንሽላሊት በእጅ ትያዛለች፤

ሆኖም በቤተ መንግሥት ትገኛለች።

29“አረማመዳቸው ግርማዊ የሆነ ሦስት ነገሮች አሉ፤

እንዲያውም በሞገስ የሚጐማለሉ አራት ናቸው፤

30ከአራዊት መካከል ኀይለኛ የሆነው፣

ከምንም ነገር ፊት ግንባሩን የማያጥፈው አንበሳ፤

31ጐርደድ ጐርደድ የሚል አውራ ዶሮ፣ አውራ ፍየል፣

እንዲሁም በሰራዊቱ የታጀበ ንጉሥ ናቸው።30፥31 ወይም ከተቃውሞ የተጠበቀ ንጉሥ

32“ተላላ ሆነህ ራስህን ከፍ ከፍ ካደረግህ፣

ወይም ክፉ ነገር ካቀድህ፣

እጅህን በአፍህ ላይ አድርግ።

33ወተት ሲናጥ ቅቤ እንደሚወጣው፣

አፍንጫን ሲያሹት እንደሚደማ፣

ቍጣን ማነሣሣትም ጥልን ይፈጥራል።”