箴言 27 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

箴言 27:1-27

1不要為明天誇口,

因為你不知明天會怎樣。

2讓別人誇獎你,不要開口自誇;

讓外人稱讚你,不要自吹自擂。

3石頭沉,沙土重,

不如愚人惹的麻煩重。

4暴怒固然殘酷,

憤恨好比狂瀾,

然而嫉妒更是無人能敵。

5開誠佈公的責備勝過隱藏的愛。

6朋友加的創傷出自真誠,

仇敵連連親吻卻是多餘。

7飽足的人連蜂蜜也嫌棄,

饑餓的人吃苦食也甘甜。

8離鄉背井的人就像離巢的飛鳥。

9膏油和香料使人暢快,

朋友的勸誡更加甘甜。

10不可拋棄你的朋友和父親的至交。

患難時別投靠兄弟,

近鄰勝過遠親。

11孩子啊,你要做智者,

使我的心喜樂,

我好回答譏笑我的人。

12明哲人遇禍躲避,

愚昧人前去受害。

13誰為陌生人作保,

就拿誰的衣服;

誰為淫婦作保,

誰就得交抵押。

14清早高聲為鄰舍祝福,

無異於咒詛他。

15喋喋不休的婦人,

就像雨天房屋漏個不停;

16想制止她猶如制止狂風,

又像用手抓油一樣困難。

17朋友互相切磋,

如鐵磨鐵越磨越利。

18看無花果樹的吃無花果,

照顧主人的也必得尊榮。

19水能映照人的面貌,

心能反映人的本相。

20陰間和死亡填不滿,

人的眼目永不滿足。

21鼎煉銀,爐煉金,

讚美也考驗人。

22就算把愚人放在臼裡與麥子一起搗碎,

他仍然難脫愚昧。

23你要瞭解你的羊群,

小心照料你的牲畜。

24因為錢財有用盡時,

冠冕不能萬代長存。

25乾草割去,嫩草長出,

山間的野草都被收起來。

26小羊的皮毛可做衣服,

賣山羊的錢可買田地,

27母山羊的奶足夠你和家人喝,

也夠養活你的僕婢。

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 27:1-27

1ነገ በሚሆነው አትመካ፤

ቀን የሚያመጣውን አታውቅምና።

2ሌላው ያመስግንህ እንጂ የገዛ አፍህ አይደለም፤

ሌላ ሰው ያወድስህ እንጂ የገዛ ከንፈርህ አይሁን።

3ድንጋይ ይከብዳል፤ አሸዋም ሸክም ነው፤

የተላላ ሰው ጕነጣ ግን ከሁለቱም ይከብዳል።

4ንዴት ጨካኝ፣ ቍጣም ጐርፍ ነው፤

በቅናት ፊት ግን ማን መቆም ይችላል?

5የተገለጠ ዘለፋ፣

ከተደበቀ ፍቅር ይሻላል።

6ከጠላት ደጋግሞ መሳም ይልቅ፣

የወዳጅ ማቍሰል ይታመናል።

7ለጠገበ ማር አይጥመውም፤

ለተራበ ግን እሬት እንኳ ይጣፍጠዋል።

8ከቤቱ ወጥቶ የሚባዝን ሰው፣

ጎጆዋን ለቅቃ እንደምትባዝን ወፍ ነው።

9ሽቱና ዕጣን ልብን ደስ ያሰኛሉ፤

የወዳጅ ማስደሰትም ከቅን ምክሩ ይመነጫል።

10የራስህንም ሆነ የአባትህን ወዳጅ አትተው፤

መከራ በሚያጋጥምህ ጊዜ ወደ ወንድምህ ቤት አትሂድ፤

ሩቅ ካለ ወንድም ቅርብ ያለ ጎረቤት ይሻላል።

11ልጄ ሆይ፤ ጠቢብ ሁን፤ ልቤን ደስ አሰኘው፤

ለሚንቁኝ ሁሉ መልስ መስጠት እችል ዘንድ።

12ጥንቁቅ አደጋን አይቶ ይሸሸጋል፤

ማስተዋል የጐደለው ግን ወደዚያው ይሄዳል፤ ይጐዳልም።

13ለማይታወቅ ሰው የተዋሰን ልብሱን ግፈፈው፤

ለዘልዛላ ሴት ከተዋሰማ ዐግተው።

14ሰው ድምፁን ከፍ አድርጎ ባልንጀራውን በማለዳ ቢመርቅ፣

እንደ ርግማን ይቈጠራል።

15ጨቅጫቃ ሚስት፣

በዝናብ ቀን እንደሚወርድ የማያቋርጥ ጠፈጠፍ ናት፤

16እርሷን ለመግታት መሞከር፣ ነፋስን እንደ መግታት ወይም ዘይትን

በእጅ እንደ መጨበጥ ነው።

17ብረት ብረትን እንደሚስል፣

ሰውም ሌላውን ሰው እንደዚሁ ይስለዋል።

18በለስን የሚንከባከብ ፍሬዋን ይበላል፤

ጌታውን የሚያገለግልም ክብርን ይጐናጸፋል።

19ውሃ ፊትን እንደሚያሳይ፣

የሰውም ልብ ማንነቱን ገልጦ ያሳያል።

20ሲኦልና የሙታን ዓለም27፥20 ወይም ሞትና ጥፋት እንደማይጠግቡ ሁሉ፣

የሰውም ዐይን አይረካም።

21ብር በማቅለጫ፣ ወርቅ በከውር እንደሚፈተን፣

ሰውም በሚቀበለው ምስጋና ይፈተናል።

22ጅልን በሙቀጫ ብትወቅጠው፣

እንደ እህልም በዘነዘና ብታደቅቀው፣

ጅልነቱን ልታስወግድለት አትችልም።

23በጎችህ በምን ሁኔታ እንዳሉ ደኅና አድርገህ ዕወቅ፤

መንጋህንም ተንከባከብ፤

24ሀብት ለዘላለም አይኖርምና፤

ዘውድም ከትውልድ ወደ ትውልድ ጸንቶ አይኖርም።

25ደረቁ ሣር ተወግዶ፣ አዲሱ ብቅ ሲል፣

በየኰረብታው ላይ ያለው ሣር ተሰብስቦ ሲገባ፣

26ከበግ ጠቦቶች ልብስ ታገኛለህ፤

ፍየሎችም የዕርሻ መሬት መግዣ ይሆኑሃል።

27አንተንና ቤተ ሰብህን፣

ገረዶችህንም ጭምር ለመመገብ፣

የተትረፈረፈ የፍየል ወተት ይኖርሃል።