箴言 23 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

箴言 23:1-35

1你若與官長同席,

要注意面對的是誰。

2如果你是貪吃的人,

就要節制食慾23·2 節制食慾」希伯來文是「把刀放在喉嚨上」。

3不可貪戀他的美食,

這美食是圈套。

4別為錢財耗盡心力,

要明智,適可而止。

5錢財眨眼之間消逝無蹤,

它必長出翅膀如鷹飛去。

6不要吃吝嗇人的飯,

不可貪圖他的美味。

7因為他總是精於算計,

嘴上說「請吃,請喝」,

心裡卻另有盤算。

8你必嘔出所吃的那點飯,

你說的美言都必枉費。

9不要和愚人說話,

他必藐視你的智言。

10不可挪移古時的界石,

不可侵佔孤兒的田地。

11因他們的救贖主強大,

祂必對付你,替他們伸冤。

12你要專心接受教誨,

側耳傾聽智言。

13不要疏於管教孩子,

杖責不會使他斃命,

14杖責能救他脫離死亡。

15孩子啊,

你若心裡有智慧,

我心裡也會歡喜。

16你的口若說正直的話,

我的內心也歡暢不已。

17不要心裡羡慕罪人,

要終日敬畏耶和華。

18這樣,你必前途光明,

你的盼望不會幻滅。

19孩子啊,聽我的話,

要有智慧,心守正道。

20不要結交酒肉朋友,

21因為好酒貪吃者必窮困,

貪睡的人必穿破衣爛衫。

22要聽從生養你的父親,

不可輕視年老的母親。

23要買真理、智慧、教誨和悟性,

不可賣掉。

24義人的父親喜樂無限,

智慧之子使父母歡欣。

25你要使父母快樂,

叫生你的人歡欣。

26孩子啊,把你的心交給我,

歡然走我的道路。

27妓女是深坑,淫婦是陷阱;

28她像強盜般埋伏,

使世間增添奸徒。

29誰有災禍?誰有憂傷?

誰有爭吵?誰有怨言?

誰無故受傷?誰兩眼發紅?

30就是那些沉迷醉鄉,

品嚐醇和之酒的人!

31雖然鮮紅的酒在杯中閃爍,

喝下去痛快,但不要盯著它。

32它終必像蛇一樣傷你,

像毒蛇一樣咬你。

33你的眼會看見怪異的景象,

你會神智不清,胡言亂語。

34你好像躺在怒海中,

又像臥在桅杆頂上。

35你會說:「人打我,我不痛;

人揍我,我不知。

什麼時候醒了,再乾一杯!」

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 23:1-35

1ከገዥ ጋር ለመብላት በምትቀመጥበት ጊዜ፣

በፊትህ ያለውን በሚገባ23፥1 ወይም ማን መሆኑን አስተውል፤

2ስግብግብም ብትሆን እንኳ፣

በጕረሮህ ላይ ካራ አጋድምበት፤

3የእርሱ ጣፋጭ መብል አያስጐምጅህ፤

ምግቡ አታላይ ነውና።

4ሀብት ለማግኘት ስትል ራስህን አታድክም፤

ሐሳብህን የመግታት ጥበብ ይኑርህ።

5በሀብት ላይ ዐይንህን ብትጥል፣

ወዲያው ይጠፋል፤

ወደ ሰማይ እንደሚበርር ንስር፣ በርግጥ ክንፍ አውጥቶ ይበርራል።

6የሥሥታምን ምግብ አትብላ፤

ጣፋጭ መብሉም አያስጐምጅህ፤

7ሁልጊዜ ስለ ዋጋ የሚያሰላ ሰው ነውና፤23፥7 ወይም በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና ወይም ግብዣ አዘጋጅቶ

“ብላ፣ ጠጣ” ይልሃል፤

ልቡ ግን ከአንተ ጋር አይደለም።

8የበላሃት ትንሿ እንኳ ታስመልስሃለች፤

የምስጋና ቃልህንም ከንቱ ታደርጋለህ።

9ከጅል ጋር አትነጋገር፤

የቃልህን ጥበብ ያንኳስሳልና።

10የጥንቱን የወሰን ምልክት አታፋልስ፤

አባት የሌላቸውንም ልጆች መሬት አትግፋ፤

11ታዳጊያቸው ብርቱ ነውና፤

እርሱ ይፋረድላቸዋል።

12ልብህን ለምክር፣

ጆሮህንም ለዕውቀት ቃል ስጥ።

13ልጅን ከመቅጣት ወደ ኋላ አትበል፤

በአርጩሜ ብትገርፈው አይሞትም።

14በአርጩሜ ቅጣው፤

ነፍሱንም ከሞት23፥14 ዕብራይስጡ ሲኦል ይላል አድናት።

15ልጄ ሆይ፤ ልብህ ጠቢብ ቢሆን፣

የእኔም ልብ ሐሤት ያደርጋል፤

16ከንፈሮችህ ትክክሉን ቢናገሩ፣

ውስጣዊ ሁለንተናዬ ሐሤት ያደርጋል።

17ልብህ በኀጢአተኞች አይቅና፤

ነገር ግን ዘወትር እግዚአብሔርን ለመፍራት ትጋ።

18ለነገ ርግጠኛ አለኝታ ይኖርሃል፤

ተስፋህም ከንቱ አይሆንም።

19ልጄ ሆይ አድምጥ፤ ጠቢብም ሁን፤

ልብህም ከትክክለኛው መንገድ አይውጣ።

20ብዙ የወይን ጠጅ ከሚጠጡ፣

ሥጋ ከሚሰለቅጡ ጋር አትወዳጅ፤

21ሰካራሞችና ሆዳሞች ድኾች ይሆናሉና፤

እንቅልፋምነትም ቡትቶ ያለብሳቸዋል።

22የወለደህን አባትህን አድምጥ፤

እናትህንም ባረጀች ጊዜ አትናቃት።

23እውነትን ግዛት እንጂ አትሽጣት፤

ጥበብን፣ ተግሣጽንና ማስተዋልን ገንዘብህ አድርግ።

24የጻድቅ ሰው አባት እጅግ ደስ ይለዋል፤

ጠቢብ ልጅ ያለውም በእርሱ ሐሤት ያደርጋል።

25አባት እናትህ ደስ ይበላቸው፤

ወላጅ እናትህም ሐሤት ታድርግ።

26ልጄ ሆይ፤ ልብህን ስጠኝ፤

ዐይኖችህም ከመንገዴ አይውጡ፤

27ዘልዛላ ሚስት ጠባብ ጕድጓድ፣

አመንዝራም ሴት ዐዘቅት ናትና፤

28እንደ ወንበዴ ታደባለች፤

በሰዎችም መካከል ወስላቶችን ታበዛለች።

29ዋይታ የማን ነው? ሐዘንስ የማን ነው?

ጠብ የማን ነው? ብሶትስ የማን ነው?

በከንቱ መቍሰል የማን ነው? የዐይን ቅላትስ የማን ነው?

30የወይን ጠጅ በመጠጣት ጊዜያቸውን ለሚያባክኑ ነው፤

እየዞሩ ድብልቅ የወይን ጠጅ ለሚቀማምሱ ሰዎች ነው።

31መልኩ ቀይ ሆኖ፣

በብርጭቆ ውስጥ ሲያንጸባርቅ፣

ሰተት ብሎ በሚወርድበትም ጊዜ፣ ወደ ወይን ጠጅ ትክ ብለህ አትመልከት።

32በመጨረሻው እንደ እባብ ይነድፋል፤

እንደ እፉኝትም መርዙን ይረጫል።

33ዐይኖችህ እንግዳ ነገር ያያሉ፤

አእምሮህም ይቀባዥራል።

34በባሕር ላይ የተኛህ፣

በመርከብ ምሰሶ ጫፍ ላይ የተጋደምህ ትመስላለህ።

35አንተም፣ “መቱኝ፤ አልተጐዳሁም፤

ደበደቡኝ፤ አልተሰማኝም፤

ታዲያ፣ ሌላ መጠጥ እንዳገኝ፣

መቼ ነው የምነቃው?” ትላለህ።