箴言 19 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

箴言 19:1-29

1行為正直的窮人,

勝過詭詐的愚人。

2熱誠卻無知不足取,

行動急躁難免有錯。

3人因愚昧而自毀前程,

他的心卻抱怨耶和華。

4財富招來許多朋友,

窮人卻遭朋友拋棄。

5作偽證者難免受罰,

撒謊的人罪責難逃。

6大家都討好慷慨的人,

人人都結交好施贈的。

7窮人被親人厭棄,

朋友都遠遠躲避。

他苦苦哀求,也無人理會。

8得到智慧的珍惜生命,

持守悟性的享受福樂。

9作偽證者難免受罰,

撒謊的人自取滅亡。

10愚人奢華宴樂不相宜,

奴隸管轄王子更離譜。

11智者不輕易發怒,

饒恕是他的榮耀。

12君王的震怒像雄獅怒吼,

君王的恩澤如草上甘露。

13愚昧之子是父親的災殃,

爭鬧之妻如雨滴漏不止。

14房屋錢財是祖先的遺產,

賢慧之妻乃耶和華所賜。

15懶惰使人沉睡,

懈怠使人挨餓。

16遵守誡命的保全性命,

藐視誡命的自尋死路。

17善待窮人等於借貸給耶和華,

耶和華必回報他的善行。

18管教孩子宜早不宜晚,

不可任由他走向滅亡。

19脾氣暴躁的人必吃苦頭。

你若救他,一次肯定不夠。

20你要受教聽勸,

以便得到智慧。

21人心中有許多計劃,

唯耶和華的旨意成就。

22人心愛慕忠誠,

受窮勝過撒謊。

23敬畏耶和華使人得享生命,

安然滿足,免遭禍患。

24懶惰人手放在餐盤,

卻懶得送食物進嘴。

25責打嘲諷者,愚人學會謹慎;

責備明哲人,他會增長見識。

26苛待父親的人可鄙,

逼走母親的人可恥。

27孩子啊,你若不聽教誨,

就會偏離知識。

28作偽證者嘲諷公義,

惡人的口吞吃罪惡。

29刑罰對付嘲諷者,

鞭子責打愚人背。

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 19:1-29

1ንግግሩ ጠማማ ከሆነ ዐጕል ሰው ይልቅ፣

ያለ ነውር የሚሄድ ድኻ ሰው ይሻላል።

2ዕውቀት አልባ የሆነ ቀናኢነት መልካም አይደለም፤

ጥድፊያም መንገድን ያስታል።

3ሰው በራሱ ተላላነት ሕይወቱን ያበላሻል፤

በልቡ ግን እግዚአብሔርን ያማርራል።

4ሀብት ብዙ ወዳጅ ታፈራለች፤

ድኻን ግን ወዳጁ ገሸሽ ያደርገዋል።

5ሐሰተኛ ምስክር ከቅጣት አያመልጥም፤

ውሸት የሚነዛም ሳይቀጣ አይቀርም።

6ብዙ ሰዎች በገዥ ዘንድ ሞገስ ለማግኘት ያሸረግዳሉ፤

ስጦታን ከሚሰጥ ሰው ጋር ሁሉም ወዳጅ ነው።

7ድኻ በሥጋ ዘመዶቹ ሁሉ የተጠላ ነው፤

ታዲያ ወዳጆቹማ የቱን ያህል ይሸሹት!

እየተከታተለ ቢለማመጣቸውም፣

ከቶ አያገኛቸውም።19፥7 ለዚህ ዐረፍተ ነገር የገባው የዕብራይስጡ ትርጓሜ በትክክል አይታወቅም።

8ጥበብን ገንዘቡ የሚያደርጋት ነፍሱን ይወድዳል፤

ማስተዋልን የሚወድዳት ይሳካለታል።

9ሐሰተኛ ምስክር ከቅጣት አያመልጥም፤

ውሸት የሚነዛም ይጠፋል።

10ተላላ ተንደላቅቆ መኖር አይገባውም፤

ባሪያ የመሳፍንት ገዥ ከሆነማ የቱን ያህል ይከፋ!

11ጥበብ ሰውን ታጋሽ ታደርገዋለች፤

በደልን ንቆ መተውም መከበሪያው ነው።

12የንጉሥ ቍጣ እንደ አንበሳ ግሣት ነው፤

በፊቱ ሞገስ ማግኘትም በሣር ላይ እንዳለ ጠል ነው።

13ተላላ ልጅ ለአባቱ መጥፊያ ነው፤

ጨቅጫቃ ሚስትም እንደማያቋርጥ ጠፈጠፍ ናት።

14ቤትና ሀብት ከወላጆች ይወረሳሉ፤

አስተዋይ ሚስት ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ናት።

15ስንፍና ከባድ እንቅልፍ ላይ ይጥላል፤

ዋልጌም ሰው ይራባል።

16ትእዛዞችን የሚያከብር ሕይወቱን ይጠብቃል፤

መንገዱን የሚንቅ ግን ይሞታል።

17ለድኻ የሚራራ ለእግዚአብሔር ያበድራል፤

ስላደረገውም ተግባር ዋጋ ይከፍለዋል።

18ገና ተስፋ ሳለ፣ ልጅህን ሥርዐት አስይዘው፤

ሲሞት ዝም ብለህ አትየው።

19ግልፍተኛ ሰው ቅጣትን መቀበል ይገባዋል፤

በምሕረት ካለፍኸው ሌላም ጊዜ አይቀርልህም።

20ምክርን ስማ፤ ተግሣጽን ተቀበል፤

በመጨረሻም ጠቢብ ትሆናለህ።

21በሰው ልብ ብዙ ሐሳብ አለ፤

የሚፈጸመው ግን የእግዚአብሔር ሐሳብ ነው።

22ሰው የሚመኘው ጽኑ ፍቅር19፥22 ወይም የሰው ሥሥት ውርደት ወይም ኀፍረት ያመጣበታል። ነው፤

ውሸታም ከመሆንም ድኻ መሆን ይሻላል።

23እግዚአብሔርን መፍራት ወደ ሕይወት ይመራል፤

እንዲህ ያለውም ሰው እፎይ ብሎ ያርፋል፤ መከራም አያገኘውም።

24ሰነፍ እጁን ከወጭቱ ያጠልቃል፤

ወደ አፉ ግን መመለስ እንኳ ይሳነዋል።

25ፌዘኛን ግረፈው፤ ብስለት የሌለውም ማስተዋልን ይማራል፤

አስተዋይን ዝለፈው፤ ዕውቀትን ይገበያል።

26አባቱን የሚዘርፍ፣ እናቱንም የሚያሳድድ፣

ዕፍረትና ውርደት የሚያመጣ ልጅ ነው።

27ልጄ ሆይ፤ እስቲ ምክርን ማዳመጥ ተው፤

ከዕውቀትም ቃል ትስታለህ።

28አባይ ምስክር በፍትሕ ላይ ያፌዛል፤

የክፉዎችም አፍ በደልን ይሰለቅጣል።

29ለፌዘኞች ቅጣት፣

ለተላሎችም ጀርባ ጅራፍ ተዘጋጅቷል።