箴言 16 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

箴言 16:1-33

1心中的策劃在於人,

應對之言來自耶和華。

2人看自己的行為都純全,

但是耶和華卻衡量人心。

3把你的事交托耶和華,

你的計劃必實現。

4耶和華所造的萬物各有其用,

連惡人也是為災難之日所造。

5耶和華厭惡心驕氣傲者,

他們必逃不過祂的責罰。

6慈愛和忠信可讓罪惡得贖,

敬畏耶和華使人遠離罪惡。

7人所行的若蒙耶和華喜悅,

耶和華必使仇敵與他和好。

8財物雖少但行事公義,

勝過家財萬貫卻不公義。

9人心中籌畫自己的道路,

但耶和華決定他的腳步。

10王口中有上帝的話,

斷案時必無差錯。

11公道的秤與天平屬於耶和華,

袋中一切的法碼由祂制定。

12君王憎恨惡行,

因王位靠公義而立。

13王喜愛公義的言詞,

器重說話正直的人。

14王的烈怒如死亡使者,

然而智者能平息王怒。

15王的笑容帶給人生命,

他的恩惠像春雨之雲。

16得智慧勝過得黃金,

獲悟性勝過獲白銀。

17正直人的大道遠離罪惡,

堅守正道的保全性命。

18驕橫是淪亡的前奏,

狂傲是敗落的預兆。

19寧可謙卑地與貧寒人相處,

也不跟狂傲人共享戰利品。

20聽從訓言的人受益匪淺,

信靠耶和華的人蒙祝福。

21智者以明辨著稱,

甜言能說服人心。

22智慧是智者的生命泉,

愚昧為愚人帶來懲罰。

23智者三思而後言,

其言使人長見識。

24良言如蜜,

使人心靈甘甜、身體康健。

25有一條路看似正確,

最終卻通向死亡。

26工人的胃口促他工作,

口腹之需是他的動力。

27不務正業的人圖謀惡事,

他的口舌如烈焰般危險。

28邪僻的人散播紛爭,

造謠的人破壞友情。

29殘暴之徒引誘鄰舍走入歧途。

30惡人眯起眼睛圖謀不軌,

歹徒咬著嘴唇策劃惡事。

31白髮是榮耀的冠冕,

行為公義方能得到。

32不輕易發怒者勝過勇士,

能自我控制勝過攻陷城池。

33人可以搖籤求問,

但耶和華決定一切。

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 16:1-33

1የልብ ዕቅድ የሰው ነው፤

የአንደበት መልስ ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

2ለሰው መንገዱ ሁሉ ንጹሕ መስሎ ይታየዋል፤

መነሻ ሐሳቡ ግን በእግዚአብሔር ይመዘናል።

3የምታደርገውን ሁሉ ለእግዚአብሔር ዐደራ ስጥ፤

ዕቅድህም ሁሉ ይሳካልሃል።

4እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር ለራሱ ዐላማ ሠርቷል፤

ክፉዎችንም እንኳ ለጥፋት ቀን አዘጋጅቷል።

5እግዚአብሔር በልብ የሚታበዩትን ሁሉ ይጸየፋል፤

እነርሱም ከቅጣት እንደማያመልጡ በርግጥ ዕወቅ።

6በፍቅርና በታማኝነት ኀጢአት ይሰረያል፤

እግዚአብሔርን በመፍራት ሰው ከክፋት ይርቃል።

7የሰው መንገድ እግዚአብሔርን ደስ ሲያሰኘው፣

ጠላቶቹ እንኳ አብረውት በሰላም እንዲኖሩ ያደርጋል።

8ከጽድቅ ጋር ጥቂቱ ነገር፣

በግፍ ከሚገኝ ብዙ ትርፍ ይሻላል።

9ሰው በልቡ መንገዱን ያቅዳል፤

እግዚአብሔር ግን ርምጃውን ይወስንለታል።

10የንጉሥ ከንፈሮች እንደ አምላክ ቃል ይናገራሉ፤

አንደበቱ ፍትሕን ያዛባ ዘንድ አይገባም።

11ሐቀኛ መስፈሪያና ሚዛን ከእግዚአብሔር ናቸው፤

በከረጢት ውስጥ ያሉት መመዘኛዎችም ሁሉ ሥራዎቹ ናቸው።

12ክፋትን ማድረግ ለነገሥታት አስጸያፊ ነው፤

ዙፋን የሚጸናው በጽድቅ ነውና።

13ነገሥታት በታማኝ ከንፈሮች ደስ ይላቸዋል፤

እውነት የሚናገረውን ሰው ይወድዱታል።

14የንጉሥ ቍጣ የሞት መልእክተኛ ነው፤

ጠቢብ ሰው ግን ቍጣውን ያበርዳል።

15የንጉሥ ፊት ሲፈካ ሕይወት አለ፤

በጎነቱም ዝናብ እንዳዘለ የበልግ ደመና ነው።

16ከወርቅ ይልቅ ጥበብን ማግኘት፣

ከብርም ማስተዋልን መምረጥ ምንኛ ይበልጣል!

17የቅኖች ጐዳና ከክፋት የራቀ ነው፤

መንገዱንም የሚጠብቅ ሕይወቱን ይጠብቃል።

18ትዕቢት ጥፋትን፣

የእብሪት መንፈስም ውድቀትን ትቀድማለች።

19በተዋረደ መንፈስ ከተጨቈኑት ጋር መሆን፣

ከትዕቢተኞች ጋር ብዝበዛን ከመካፈል ይሻላል።

20ምክርን የሚሰማ ይለመልማል፤

በእግዚአብሔርም የሚታመን ቡሩክ ነው።

21ልባቸው ጠቢብ የሆነ አስተዋዮች ይባላሉ፤

ደስ የሚያሰኙ ቃላትም ዕውቀትን ያዳብራሉ።16፥21 ወይም ቃላትም ተደማጭነት ያስገኛሉ

22ማስተዋልን ገንዘብ ላደረጋት የሕይወት ምንጭ ናት፤

ቂልነት ግን በተላሎች ላይ ቅጣት ታመጣባቸዋለች።

23የጠቢብ ሰው ልብ አንደበቱን ይመራል፤

ከንፈሮቹም ዕውቀትን ያዳብራሉ።16፥23 ወይም አንደበቱን አሳማኝ ያደርጋሉ

24ደስ የሚያሰኝ ቃል የማር ወለላ ነው፤

ለነፍስ ጣፋጭ፣ ለዐጥንትም ፈውስ ነው።

25ለሰው ቀና መስሎ የሚታይ መንገድ አለ፤

በመጨረሻ ግን ወደ ሞት ይመራል።

26ሠራተኛን የዕለት ጕርስ ፍላጎቱ ታታሪ ያደርገዋል፤

ራቡም ይገፋፋዋል።

27ወራዳ ሰው ክፋትን ያውጠነጥናል፤

ንግግሩም እንደሚለበልብ እሳት ነው።

28ጠማማ ሰው ጠብን ይዘራል፤

ሐሜተኛም የቅርብ ወዳጆችን ይለያያል።

29ክፉ ሰው ባልንጀራውን ያባብለዋል፤

መልካም ወዳልሆነውም መንገድ ይመራዋል።

30በዐይኑ የሚጠቅስ ሰው ጠማማነትን ያውጠነጥናል፤

በከንፈሩ የሚያሽሟጥጥም ወደ ክፋት ያዘነብላል።

31ሽበት የክብር ዘውድ ነው፤

የሚገኘውም በጽድቅ ሕይወት ነው።

32ታጋሽ ሰው ከጦረኛ፣

ስሜቱን የሚገዛም ከተማን በጕልበቱ ከሚይዝ ይበልጣል።

33ዕጣ በጕያ ውስጥ ይጣላል፤

ውሳኔው በሙሉ ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።