申命記 30 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

申命記 30:1-20

歸向耶和華必蒙福

1「當我向你們陳明的這些祝福和咒詛都應驗在你們身上時,如果你們在你們的上帝耶和華驅逐你們去的各國中回想這些話, 2歸向你們的上帝耶和華,你們及子孫照我今天的吩咐全心全意地聽從祂的話, 3祂必改變你們被擄的境遇,憐憫你們,把你們從祂驅逐你們去的列國招聚回來。 4即使你們被驅逐到天涯,你們的上帝耶和華也會把你們帶回來, 5帶到你們祖先的土地上,使你們擁有那片土地,比你們祖先更加人丁興旺、繁榮昌盛。 6你們的上帝耶和華要潔淨你們和你們子孫的心,好讓你們全心全意地愛祂,並且存活。 7你們的上帝耶和華要把所有的咒詛加在你們的仇敵及憎惡你們、迫害你們的人身上。 8你們必再次聽從耶和華,遵行今天祂藉我吩咐你們的一切誡命。 9-10倘若你們聽從你們的上帝耶和華的話,遵守這律法書上的誡命和律例,全心全意地歸向祂,祂必使你們凡事蒙福、兒女眾多、牛羊成群、五穀豐登。因為祂必樂意再次賜福你們,像從前賜福你們祖先一樣。

生死抉擇

11「我今天頒佈給你們的誡命,對你們來說不難遵行,也非遙不可及。 12這誡命並非在天上,以致你們說,『誰替我們上天取下來,講給我們聽,讓我們遵行呢?』 13這誡命也不在海的彼岸,以致你們說,『誰替我們過海取來,講給我們聽,好讓我們遵行呢?』 14這誡命近在咫尺,就在你口裡,在你心中,好讓你們遵行。

15「看啊,今天我把生死禍福擺在你們面前。 16我今天吩咐你們要愛你們的上帝耶和華,遵行祂的旨意,遵守祂的誡命、律例和典章,以便你們可以存活,人口興旺,在你們將要佔領的土地上蒙祂賜福。 17但倘若你們心中偏離,不肯聽從,被引誘去祭拜、供奉別的神明, 18我今天警告你們,你們必定滅亡,在約旦河對岸——你們將要佔領的土地上無法長久。 19今天,我叫天地為你們作證,我已把生死禍福擺在你們面前。選擇生命吧,以便你們及子孫可以存活。 20要愛你們的上帝耶和華,聽從祂的話,倚靠祂,因為祂是你們的生命,祂必使你們長久住在祂起誓賜給你們祖先亞伯拉罕以撒雅各的土地上。」

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 30:1-20

ወደ እግዚአብሔር በመመለስ የሚገኝ በረከት

1በፊትህ ያስቀመጥሁት ይህ በረከትና መርገም ሁሉ በአንተ ላይ ሲመጣና አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በትኖህ በምትኖርበት አሕዛብ መካከል ሆነህ ወደ ልብህ ተመልሰህ ነገሮቹን በምታስተውልበት ጊዜ፣ 2እንዲሁም ዛሬ እኔ በማዝዝህ ሁሉ መሠረት አንተና ልጆችህ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ተመልሳችሁ በፍጹም ልባችሁና በፍጹም ነፍሳችሁ እርሱን ስትታዘዙ፣ 3አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ምርኮህን ይመልስልሃል30፥3 ወይም፣ ከግዞት ይመልስሃል፤ ይራራልሃልም፤ አንተን ከበተነበት አሕዛብ መካከልም እንደ ገና ይሰበስብሃል። 4ከሰማይ በታች እጅግ ሩቅ ወደ ሆነ ምድር ብትጋዝ እንኳ፣ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ከዚያ ይሰበስብሃል፤ መልሶም ያመጣሃል። 5የአባቶችህ ወደ ሆነችው ምድር ያመጣሃል፤ አንተም ትወርሳታለህ። ከአባቶችህ ይበልጥ ያበለጽግሃል፤ ያበዛሃልም። 6አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) በፍጹም ልብህና በፍጹም ነፍስህ እንድትወድደው፣ በሕይወትም እንድትኖር፣ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የአንተንና የዘርህን ልብ ይገርዛል። 7አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ይህን ርግማን ሁሉ በሚጠሉህና በሚያሳድዱህ ጠላቶችህ ላይ ያደርገዋል። 8አንተም ተመልሰህ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ትታዘዛለህ፤ ዛሬ እኔ የማዝዝህን ትእዛዝ ሁሉ ትጠብቃለህ። 9ከዚያም አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በእጅህ ሥራ ሁሉና በወገብህ ፍሬ፣ በእንስሳትህ ግልገሎችና በምድርህ ሰብል እጅግ ያበለጽግሃል። በአባቶችህ ደስ እንደ ተሰኘ ሁሉ፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) አንተንም በማበልጸግ ደስ ይለዋልና። 10ይህም የሚሆነው፣ አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) ከታዘዝህና በዚህ የሕግ መጽሐፍ የተጻፉትን ትእዛዙንና ሥርዐቱን በመጠበቅ፣ በፍጹም ልብህና በፍጹም ነፍስህ ወደ አምላክህ ወደ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ስትመለስ ነው።

ሕይወትን ወይም ሞትን ስለ መምረጥ

11በዛሬው ዕለት የምሰጥህ ትእዛዝ ይህን ያህል አስቸጋሪ ወይም ከአንተ የራቀች አይደለችም። 12“እንድንፈጽማት አምጥቶ ይነግረን ዘንድ፣ ማን ወደ ሰማይ ይወጣል?” እንዳትል፣ በላይ በሰማይ አይደለችም። 13ደግሞም፣ “እንድናደርጋት አምጥቶ ይነግረን ዘንድ፣ ማን ባሕሩን ይሻገራል?” እንዳትልም፣ ከባሕር ማዶ አይደለችም። 14ነገር ግን ቃሉ ለአንተ በጣም ቅርብ ነው፤ ታደርገውም ዘንድ በአፍህና በልብህ ውስጥ ነው።

15እነሆ፤ ዛሬ ሕይወትንና በረከትን፣ ሞትንና ጥፋትን በፊትህ አኑሬአለሁ። 16አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) እንድትወድ፣ በመንገዱም እንድትሄድና ትእዛዙን፣ ሥርዐቱንና ሕጉን እንድትጠብቅ አዝዝሃለሁ፤ ከዚያም በሕይወት ትኖራለህ፤ ትበዛለህም፤ አምላክህም እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ትወርሳት ዘንድ በምትገባበት ምድር ይባርክሃል።

17ዳሩ ግን ልብህ ወደ ኋላ ቢመለስና ባትታዘዝ፣ ለሌሎች አማልክት ለመስገድ ብትታለልና ብታመልካቸው፣ 18በርግጥ እንደምትጠፉ እኔ በዛሬው ዕለት እነግራችኋለሁ፤ ዮርዳኖስን ተሻግረህ ትወርሳት ዘንድ በምትገባባት ምድር ብዙ አትኖሩባትም።

19ሕይወትንና ሞትን፣ በረከትንና ርግማንን በፊትህ እንዳስቀመጥሁ ዛሬ ሰማይንና ምድርን ምስክር አድርጌ እጠራብሃለሁ። እንግዲህ አንተና ልጆችህ በሕይወት እንድትኖሩ ሕይወትን ምረጥ፤ 20ይኸውም አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) እንድትወድ፣ ቃሉን እንድታደምጥና ከእርሱ ጋር እንድትጣበቅ ነው። ምክንያቱም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሕይወትህ ነው፤ ለአባቶችህ ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ ሊሰጣቸው በማለላቸው ምድር ረዥም ዕድሜ ይሰጥሃል።