申命記 19 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

申命記 19:1-21

設立避難城

1「你們的上帝耶和華毀滅那些民族,把他們的土地賜給你們,使你們趕走他們,住進他們的城邑和房屋後, 2-3你們要把土地劃分為三個地區,在每個地區設立一座避難城,修好通往這三座城的道路,以便誤殺人者可以逃往最近的避難城。

4「如果有人無意間殺了素無冤仇的同伴,他可以逃往避難城,以保住性命。 5例如,有人和朋友去森林砍樹,斧頭脫柄,誤殺了朋友,他就可以逃往避難城,以保住性命。 6否則,如果避難城離誤殺人者太遠,怒火中燒的報仇者就會追上去殺死他。其實他是不該死的,因為他與被誤殺的人素無冤仇。 7因此,我吩咐你們要設立三座避難城。

8-9「如果你們謹遵我今天吩咐你們的這一切誡命,愛你們的上帝耶和華,一生遵行祂的旨意,祂就會按照祂對你們祖先所起的誓,擴張你們的疆域,把應許給你們祖先的土地賜給你們。那時,你們要再設三座避難城, 10免得無辜人的血流在你們的上帝耶和華賜給你們作產業之地,以致你們擔當枉殺無辜的罪。

11「如果有人因憎恨鄰居而暗中埋伏,殺了鄰居,然後逃到避難城, 12他本城的長老要派人去把他帶回來,交給復仇的人,將他處死。 13不可憐憫他,要從以色列除掉這種濫殺無辜的罪,這樣你們才會順利。

14「在你們的上帝耶和華將要賜給你們作產業之地,你們不可挪動鄰居的界石,因為那是先人立的。

15「如果人犯了什麼罪或有什麼過失,不可憑一個證人作證就定罪,要有兩三個證人才可以定案。 16如果有人作偽證誣陷別人, 17訴訟雙方要站在耶和華面前,讓當值的祭司和審判官定奪。 18審判官要仔細審查案件,如果發現那人作偽證, 19就要按照他企圖加給被誣告者的傷害處罰他。這樣,就從你們當中除掉了罪惡。 20其他人聽說後,都會害怕,不敢再做這種惡事。 21你們對惡人不可心軟,要以命償命,以眼還眼,以牙還牙,以手還手,以腳還腳。

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 19:1-21

መማጸኛ ከተሞች

19፥1-14 ተጓ ምብ – ዘኍ 35፥6-34ዘዳ 4፥41-43ኢያ 20፥1-9

1አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ምድራቸውን ለአንተ የሚሰጥባቸውን አሕዛብ በሚደመስሳቸው ጊዜና አንተም እነርሱን አስለቅቀህ በከተሞቻቸውና በቤቶቻቸው በምትቀመጥበት ጊዜ፣ 2አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ርስት አድርጎ በሚሰጥህ ምድር አማካይ ስፍራ፣ ሦስት ከተሞችን ለራስህ ለይ። 3ሰው የገደለ ሁሉ እንዲሸሽባቸው አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ርስት አድርጎ በሚሰጥህ ምድር መንገዶችን ሠርተህ፣ በሦስት ክፈላቸው።

4በተንኰል ሳይሆን ድንገት ሳያስበው ባልንጀራውን ገድሎ ሕይወቱን ለማትረፍ ለሚሸሽ ሰው መመሪያው የሚከተለው ነው። 5እነሆ፤ አንድ ሰው ከባልንጀራው ጋር ዕንጨት ለመቍረጥ ወደ ጫካ ቢሄድ፣ ዛፉን ለመጣል መጥረቢያውን በሚሰነዝርበት ጊዜ ብረቱ ከእጀታው ወልቆ ባልንጀራውን በመምታት ቢገድለው፣ ያ ሰው ከእነዚህ ከተሞች ወደ አንዱ በመሸሽ ሕይወቱን ማትረፍ ይችላል። 6አለዚያ በተንኰል ሳይሆን ድንገት ሳያስበው ባልንጀራውን ቢገድል፣ መንገዱ ረዥም ከሆነ ደም ተበቃዩ በንዴት ተከታትሎ ይደርስበትና መገደል የማይገባውን ሰው ሊገድል ይችላል። 7ሦስት ከተሞችን ለራስህ እንድትለይ ያዘዝሁህ በዚሁ ምክንያት ነው።

8ለአባቶችህ በመሐላ በገባላቸው ቃል መሠረት፣ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ወሰንህን ሲያሰፋውና ለእነርሱ በሰጣቸው መሠረት ምድሪቷን ሁሉ ሲሰጥህ፣ 9አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) እንድትወድድና ምንጊዜም በመንገዱ እንድትሄድ ዛሬ የማዝዝህን እነዚህን ሕግጋት ሁሉ በጥንቃቄ የምትጠብቅ ከሆነ፣ በእነዚህ ላይ ሌሎች ሦስት ከተሞችን ትጨምራለህ። 10አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ርስት አድርጎ በሚሰጥህ ምድር የንጹሕ ሰው ደም እንዳይፈስስና በሚፈስሰውም ደም በደለኛ እንዳትሆን ይህን አድርግ።

11ይሁን እንጂ አንድ ሰው ባልንጀራውን ቢጠላው፣ አድፍጦ ጥቃት ቢያደርስበት፣ ቢገድለውና ከእነዚህ ከተሞች ወደ አንዲቱ ቢሸሽ፣ 12የሚኖርባት ከተማ ሽማግሌዎች ሰው ልከው ከከተማው ያስመጡት፤ እንዲገድለውም ለደም ተበቃዩ አሳልፈው ይስጡት።

13አትራራለት፤ ነገር ግን መልካም እንዲሆንልህ የንጹሑን ደም በደል ከእስራኤል አስወግድ።

14አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እንድትወርሳት በሚሰጥህ ምድር ውስጥ ለአንተ በሚተላለፍልህ ርስት ላይ የቀድሞ ሰዎች ያስቀመጡትን የባልንጀራህን የድንበር ምልክት አታንሣ።

ምስክሮች

15በማንኛውም ወንጀል ወይም ሕግ በመተላለፍ ሰውን ጥፋተኛ ለማድረግ፣ አንድ ምስክር አይበቃም፤ ጕዳዩ በሁለት ወይም በሦስት ሰዎች ምስክርነት መረጋገጥ አለበት።

16ተንኰለኛ የሆነ ምስክር አንድን ሰው በሐሰት ቢከስስ፣ 17ክርክሩ የሚመለከታቸው ሁለቱ ሰዎች በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት፣ በዚያ ወቅት በሚያገለግሉት ካህናትና ፈራጆች ፊት ይቁሙ። 18ፈራጆችም ጕዳዩን በጥልቅ ይመርምሩት፤ ያም ምስክር በወንድሙ ላይ በሐሰት የመሰከረ መሆኑ ከተረጋገጠ፣ 19በወንድሙ ላይ ለማድረግ ያሰበውን በእርሱ ላይ አድርጉበት፤ ክፉውን ከመካከልህ አስወግድ። 20የቀሩትም ሰዎች ይህን ሰምተው ይፈራሉ፤ እንዲህ ያለው ክፉ ነገርም ለወደፊቱ በመካከልህ ከቶ አይደገምም። 21ርኅራኄ አታድርግ፤ ሕይወት በሕይወት፣ ዐይን በዐይን፣ ጥርስ በጥርስ፣ እጅ በእጅ፣ እግር በእግር ይመለስ።