猶大書 1 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

猶大書 1:1-25

1我是耶穌基督的奴僕、雅各的兄弟猶大,現在寫信給蒙父上帝呼召、眷愛、被耶穌基督看顧的人。

2願上帝豐豐富富地賜給你們憐憫、平安和慈愛!

捍衛真道

3親愛的弟兄姊妹,我一直迫切地想寫信跟你們談談我們所共享的救恩,但現在我覺得有必要寫信勸勉你們竭力護衛一次就完整地交給聖徒的真道。 4因為有些不敬虔的人偷偷地混進你們中間,以上帝的恩典作藉口,放縱情慾,否認獨一的主宰——我們的主耶穌基督。聖經上早已記載,這樣的人必受到審判。

前車之鑑

5以下的事情,你們雖然都知道,但我還要再提醒你們:從前上帝1·5 上帝」有些抄本作「主」。把祂的子民從埃及救出來,後來把其中不信的人滅絕了。 6至於不守本分、擅離崗位的天使,上帝也用鎖鏈將他們永遠囚禁在幽暗裡,等候最後審判的大日子到來。 7此外,所多瑪蛾摩拉及其附近城鎮的人同樣因為荒淫無度、沉溺於變態的情慾而遭到永火的刑罰。這些事都成為我們的警戒。

假教師的惡行

8同樣,這些作夢的人玷污自己的身體,不服權柄,褻瀆有尊榮的。 9當天使長米迦勒摩西的屍體跟魔鬼爭辯的時候,尚且不敢用毀謗的話譴責牠,只說:「願主責罰你!」 10這些人卻毀謗自己不明白的事,像沒有理性的野獸一樣憑本能行事,結果自取滅亡。 11他們大禍臨頭了!他們步了該隱的後塵,為謀利而重蹈巴蘭的謬誤,又像可拉一樣因叛逆而滅亡。 12這些人在你們的愛宴中是敗類1·12 敗類」希臘文是「暗礁」或「污點」的意思。。他們肆無忌憚地吃喝,是只顧餵養自己的牧人;是沒有雨的雲,隨風飄蕩;是深秋不結果子的樹,被連根拔起,徹底枯死。 13他們是海中的狂濤,翻動著自己可恥的泡沫,是流蕩的星星,有幽幽黑暗永遠留給他們。

14亞當的第七代子孫以諾曾經針對這些人說預言:「看啊!主率領祂千萬的聖者一同降臨, 15要審判所有的人,按不虔不敬的罪人所行的惡事和他們褻瀆上帝的話定他們的罪。」 16這些人滿腹牢騷,怨天尤人,放縱自己的邪情私慾。他們口出狂言,為了謀利而阿諛奉承他人。

牢記警告

17親愛的弟兄姊妹,要謹記主耶穌基督的使徒從前給你們的警告。 18他們曾對你們說:「末世的時候,必定有不敬虔、好譏笑的人放縱自己的邪情私慾。」 19這些人製造分裂,血氣用事,心中沒有聖靈。

20親愛的弟兄姊妹,你們要在至聖的真道上造就自己,在聖靈的引導下禱告, 21常在上帝的愛中,等候我們主耶穌基督施憐憫賜給你們永生。

22那些心存疑惑的人,你們要憐憫他們; 23有些人,你們要將他們從火中搶救出來;還有些人,你們要懷著畏懼的心憐憫他們,甚至要厭惡被他們的邪情私慾玷污的衣服。

祝頌

24願榮耀歸給我們的救主——獨一的上帝!祂能保守你們不失足犯罪,使你們無瑕無疵、歡歡喜喜地站在祂的榮耀面前。 25願榮耀、威嚴、能力和權柄藉著我們的主耶穌基督都歸給祂,從萬世以前直到現今,一直到永永遠遠。阿們!

New Amharic Standard Version

ይሁዳ 1:1-25

1የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይና የያዕቆብ ወንድም ይሁዳ፤

ለተጠሩት፣ በእግዚአብሔር አብ ለተወደዱትና በኢየሱስ ክርስቶስ ለተጠበቁት1፥1 ወይም የተጠበቁት ሊሆን ይችላል

2ምሕረት፣ ሰላምና ፍቅር ይብዛላችሁ።

የዐመፀኞች ኀጢአትና የሚጠብቃቸው ፍርድ

3ወዳጆች ሆይ፤ አብረን ስለምንካፈለው ድነት ልጽፍላችሁ እጅግ ጓጕቼ ነበር፤ ነገር ግን ለቅዱሳን አንዴና ለመጨረሻ ስለ ተሰጠው እምነት እንድትጋደሉ ለመምከር እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ። 4ከረዥም ጊዜ በፊት ለዚህ ፍርድ1፥4 ወይም ፍርድ የተወሰነባቸውን ሰዎች የተጻፉ አንዳንድ ሰዎች ሾልከው ወደ እናንተ ገብተዋልና፤ እነርሱ ፈሪሀ እግዚአብሔር የሌላቸው፣ የአምላካችንን ጸጋ በርኩሰት የሚለውጡና እርሱ ብቻ ልዑል ገዣችንና ጌታችን የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚክዱ ናቸው።

5ምንም እንኳ አስቀድማችሁ ይህን ሁሉ የምታውቁ ቢሆንም፣ ጌታ1፥5 አንዳንድ የጥንት ቅጆች ኢየሱስ ይላሉ። ሕዝቡን ከግብፅ ምድር እንዴት እንዳወጣ፣ በኋላ ግን ያላመኑትን እንዳጠፋ ላስታውሳችሁ እወድዳለሁ። 6የሥልጣን ስፍራቸውን ያልጠበቁትን፣ ነገር ግን መኖሪያቸውን የተዉትን መላእክት በዘላለም እስራት እስከ ታላቁ ቀን ፍርድ ድረስ በጨለማ ጠብቋቸዋል። 7እንዲሁም ሰዶምና ገሞራ፣ በዙሪያቸውም ያሉ ከተሞች ለሴሰኝነትና ከተፈጥሮ ሥርዐት ውጭ ለሆነ ሩካቤ ሥጋ ራሳቸውን አሳልፈው ሰጡ፤ እነርሱም በዘላለም እሳት በመቀጣት ለሚሠቃዩት ምሳሌ ሆነዋል።

8በዚህ ሁኔታ እነዚህ ሕልም ዐላሚዎች የገዛ ሥጋቸውን ያረክሳሉ፤ ሥልጣንን ይቃወማሉ፤ በሰማይ ክብር ያላቸውንም ፍጥረታት ይሳደባሉ። 9የመላእክት አለቃ የሆነው ሚካኤል እንኳ ስለ ሙሴ ሥጋ ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ፣ “ጌታ ይገሥጽህ” አለው እንጂ የስድብ ቃል በመናገር ሊከስሰው አልደፈረም። 10እነዚህ ሰዎች ግን የማያውቁትን ነገር ሁሉ ይሳደባሉ፤ አእምሮ እንደሌላቸው እንስሳት በደመ ነፍስ በሚያወቁት ነገር ይጠፋሉ።

11ወዮላቸው! በቃየን መንገድ ሄደዋል፤ ለገንዘብ ሲስገበገቡ በበለዓም ስሕተት ውስጥ ወድቀዋል፤ በቆሬም ዐመፅ ጠፍተዋል።

12እነዚህ ሰዎች በፍቅር ግብዣችሁ ላይ ያለ አንዳች ኀፍረት ከእናንተ ጋር ቀርበው የሚበሉ ነውረኞች ናቸው፤ ደግሞም ራሳቸውን ብቻ የሚመግቡ እረኞች ናቸው፤ እነርሱም በነፋስ የሚነዱ ዝናብ የሌላቸው ደመናዎች ናቸው፤ በመከር ወራት ፍሬ የማይገኝባቸው ከሥራቸው ተነቅለው ሁለት ጊዜ የሞቱ ዛፎች ናቸው። 13የነውራቸውን ዐረፋ የሚደፍቁ የተቈጡ የባሕር ማዕበል፣ ድቅድቅ ጨለማ ለዘላለም የሚጠብቃቸው ተንከራታች ከዋክብት ናቸው።

14ከአዳም ጀምሮ ሰባተኛ የሆነው ሄኖክ ስለ እነዚህ ሰዎች እንዲህ ሲል ተንብዮአል፤ “እነሆ፤ ጌታ ከእልፍ አእላፋት ቅዱሳኑ ጋር ይመጣል፤ 15ይህም፣ በሰው ሁሉ ላይ ለመፍረድ እንዲሁም ዐመፀኞችን ሁሉ በክፋት መንገድ በሠሩት የዐመፅ ሥራና በክፋት በእርሱ ላይ ስለ ተናገሩት የስድብ ቃል ሁሉ አጥፊነታቸውን ይፋ ለማድረግ ነው።” 16እነዚህ ሰዎች የሚያጕረመርሙና ሌሎችን ሰዎች የሚከስሱ ናቸው፤ ርኩስ ምኞታቸውን ይከተላሉ፤ በራሳቸው ይታበያሉ፤ ጥቅም ለማግኘት ሲሉም ሌሎችን ይክባሉ።

ጸንቶ ስለ መቆም የቀረበ ጥሪ

17ነገር ግን ወዳጆች ሆይ፤ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት አስቀድመው የተናገሩትን አስታውሱ። 18እነርሱም፣ “በመጨረሻው ዘመን ርኩስ ምኞታቸውን የሚከተሉ ዘባቾች ይመጣሉ” ብለዋችኋል። 19እነዚህ ሰዎች በመካከላችሁ መለያየትን የሚፈጥሩ፣ በደመ ነፍስ የሚነዱና መንፈስ የሌላቸው ናቸው።

20እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፤ እጅግ ቅዱስ በሆነው እምነታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ ትጉ፤ በመንፈስ ቅዱስም ጸልዩ። 21ወደ ዘላለም ሕይወት የሚያደርሳችሁን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ ሳለ፣ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ።

22ተጠራጣሪ ለሆኑት ራሩላቸው፤ 23አንዳንዶችን ከእሳት ነጥቃችሁ አድኗቸው፤ ለሌሎች ደግሞ በርኩስ ሥጋ የተበከለውን ልብሳቸውን እንኳ እየጠላችሁ በፍርሀት ምሕረት አሳዩአቸው።

ቃለ ውዳሴ

24እንዳትወድቁ ሊጠብቃችሁና ያለ ነቀፋና በደስታ በክብሩ ፊት ሊያቀርባችሁ ለሚችለው፣ 25እርሱ ብቻ አዳኛችን ለሆነው አምላክ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ከዘመናት ሁሉ በፊት፣ አሁንና እስከ ዘላለምም ድረስ ክብር፣ ግርማ፣ ኀይልና ሥልጣን ይሁን፤ አሜን።