歷代志上 16 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

歷代志上 16:1-43

1眾人將上帝的約櫃抬進去,安放在大衛所搭的帳篷裡,然後在上帝面前獻上燔祭和平安祭。 2大衛獻上燔祭和平安祭後,就奉耶和華的名給民眾祝福, 3又給以色列男女每人一個餅、一塊肉和一個葡萄餅。

4大衛指派一些利未人在耶和華的約櫃前事奉,頌揚、稱謝和讚美以色列的上帝耶和華。 5為首的是亞薩,其次是撒迦利雅雅薛示米拉末耶歇瑪他提雅以利押比拿雅俄別·以東耶利,他們鼓瑟彈琴,亞薩敲鈸。 6比拿雅雅哈悉兩位祭司在上帝的約櫃前吹號。

大衛的頌歌

7那一天,大衛初次指派亞薩和他的親族唱詩歌頌耶和華,說:

8「你們要稱謝耶和華,

呼求祂的名,

在列邦傳揚祂的作為。

9要歌頌、讚美祂,

述說祂一切奇妙的作為。

10要以祂的聖名為榮,

願尋求耶和華的人都歡欣。

11要尋求耶和華和祂的能力,

時常來到祂面前。

12-13祂僕人以色列的後裔啊,

祂所揀選的雅各的子孫啊,

要記住祂所行的神蹟奇事和祂口中的判詞。

14「祂是我們的上帝耶和華,

祂在普天下施行審判。

15你們要永遠銘記祂的約,

要思想祂的應許直到千代,

16就是祂與亞伯拉罕所立的約,

以撒所起的誓。

17祂將這約定為律例賜給雅各

定為永遠的約賜給以色列

18祂說,『我必把迦南賜給你,

作為你的產業。』

19「那時他們人丁稀少,

在當地寄居,

20他們在異國他鄉流離飄零。

21耶和華不容人壓迫他們,

還為他們的緣故責備君王,

22說,『不可難為我膏立的人,

也不可傷害我的先知。』

23「普天下都要歌頌耶和華,

要天天傳揚祂的救恩;

24要在列國述說祂的榮耀,

在萬民中述說祂的奇妙作為。

25因為耶和華無比偉大,

當受至高的頌揚;

祂超越一切神明,

當受敬畏。

26列邦的神明都是假的,

唯獨耶和華創造了諸天。

27祂尊貴威嚴,

祂的聖所充滿能力和喜樂。

28「萬族萬民啊,

要把榮耀和能力歸給耶和華,

歸給耶和華!

29要將耶和華當得的榮耀歸給祂,

要將供物獻給祂,

要穿上聖潔的衣服敬拜祂。

30普天下要在祂面前戰抖;

祂堅立世界,使它不致搖動。

31願天歡喜,願地快樂;

願他們向列國宣告,

『耶和華是王!』

32願海洋和其中的萬物都歡呼,

願田野和其中的一切都歡騰!

33那時,林中的樹木都要在耶和華面前歡唱,

因為祂要來審判天下。

34要稱謝耶和華,

因為祂是美善的,

祂的慈愛永遠長存!

35「要說,『拯救我們的上帝啊,

求你救我們,招聚我們,

從列國把我們救出來,

我們好稱謝你的聖名,

以讚美你為榮。』

36從亙古到永遠,

以色列的上帝耶和華當受稱頌!」

眾民都說:「阿們」,

並讚美耶和華。

分派事奉的人員

37大衛亞薩及其親族天天在約櫃前事奉耶和華,盡當盡的職分; 38又派俄別·以東及其六十八位親族、何薩耶杜頓的兒子俄別·以東守門; 39並派祭司撒督及其他祭司在基遍高地的耶和華的聖幕前供職, 40按照耶和華在律法書上對以色列人的吩咐,每日早晚在祭壇上獻燔祭給耶和華。 41與他們一同供職的有希幔耶杜頓和其他人,他們被特別選出來稱謝上帝,因為祂有永恆的慈愛。 42希幔耶杜頓負責用號、鈸及其他樂器伴奏歌頌上帝。耶杜頓的子孫負責守門。 43於是,眾民各自回家,大衛也回去為家人祝福。

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 16:1-43

1ከዚያም የእግዚአብሔርን ታቦት አምጥተው ዳዊት በተከለለት ድንኳን ውስጥ አኖሩት፤ የሚቃጠል መሥዋዕትና የኅብረት መሥዋዕትም16፥1 በዚህና በቍጥር 2 ላይ በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል። በእግዚአብሔር ፊት አቀረቡ። 2ዳዊት የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የኅብረቱን መሥዋዕት ከሠዋ በኋላ፣ ሕዝቡን በእግዚአብሔር ስም ባረከ። 3ከዚያም ለእስራኤል ሁሉ ለወንዱም ለሴቱም አንዳንድ ሙልሙል ዳቦ፣ አንዳንድ ጥፍጥፍ ተምር፣ ሙዳ ሙዳ ሥጋና አንዳንድ ጥፍጥፍ ዘቢብ ሰጠ።

4በእግዚአብሔር ታቦት ፊት እንዲያገለግሉና ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ልመና፣ ምስጋናና ውዳሴ እንዲያቀርቡ ከሌዋውያን ሰዎች ሾመ፤ 5አለቃው አሳፍ ነበረ፤ ከእርሱ ቀጥሎ ዘካርያስ ሁለተኛ ሆኖ ተሾመ፤ ከዚያም ይዒኤል፣ ሰሚራሞት፣ ይሒኤል፣ መቲትያ፣ ኤልያብ፣ በናያስ፣ ዖቤድኤዶም፣ ይዒኤል ተሾሙ፤ እነርሱም በመሰንቆና በበገና ይዘምሩ ነበር፤ አሳፍ ደግሞ ጸናጽል የሚጸነጽል ሆኖ ተመደበ። 6እንዲሁም ካህናቱ በናያስና የሕዚኤል ዘወትር በእግዚአብሔር የኪዳኑ ታቦት ፊት መለከት እንዲነፉ ተመደቡ።

የዳዊት የምስጋና መዝሙር

16፥8-22 ተጓ ምብ – መዝ 105፥1-15

16፥23-33 ተጓ ምብ – መዝ 96፥1-13

16፥34-36 ተጓ ምብ – መዝ 106፥147-48

7በዚያም ቀን ዳዊት በመጀመሪያ ለአሳፍና ለሥራ ጓደኞቹ ይህን የእግዚአብሔር ምስጋና መዝሙር ሰጠ፤

8ለእግዚአብሔር ምስጋና አቅርቡ፤ ስሙንም ጥሩ፤

ለአሕዛብ ያደረገውን ሁሉ ንገሩ፤

9ዘምሩለት፤ ውዳሴም አቅርቡለት፤

ድንቅ ሥራውን ሁሉ ንገሩ፤

10በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤

እግዚአብሔርን የሚፈልጉ ሁሉ፣ ልባቸው ሐሤት ያድርግ።

11ወደ እግዚአብሔርና ወደ ኀይሉ ተመልከቱ፤

ዘወትር ፊቱን ፈልጉ።

12ያደረጋቸውን ድንቅ ሥራዎች፣

ታምራቱንና የሰጠውንም ፍርድ አስታውሱ፤

13እናንተ የባሪያው የእስራኤል ዘሮች፣

እናንተ የተመረጣችሁ የያዕቆብ ልጆች።

14እርሱ እግዚአብሔር አምላካችን ነው፤

ፍርዱም በምድር ሁሉ ላይ ነው፤

15ኪዳኑን እስከ ዘላለም፣

ያዘዘውንም ቃል እስከ ሺሕ ትውልድ ያስባል።

16ከአብርሃም ጋር የገባውን ቃል ኪዳን፣

ለይስሐቅ የማለውን መሐላ።

17ይህንም ለያዕቆብ ሥርዐት አድርጎ አጸና፤

ለእስራኤልም የዘላለም ኪዳን አደረገ፤

18እንዲህ ሲል፣ “የምትወርሰው ርስት እንዲሆን፣

የከነዓንን ምድር ለአንተ እሰጣለሁ።”

19ቍጥራቸው ገና ጥቂት ሳለ፣

በርግጥ ጥቂትና መጻተኞች ሳሉ፣

20ከአንዱ ሕዝብ ወደ ሌላው ሕዝብ፣

ከአንዱም መንግሥት ወደ ሌላው መንግሥት ተንከራተቱ።

21ማንም እንዲጨቍናቸው አልፈቀደም፤

ስለ እነርሱም ነገሥታትን ገሠጸ፤

22እንዲህ ሲል፤ “የቀባኋቸውን አትንኩ፤

በነቢያቴ ላይ ክፉ አታድርጉ።”

23ምድር ሁሉ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤

ማዳኑንም ዕለት ዕለት ዐውጁ።

24ክብሩን ለአሕዛብ ተናገሩ፤

ድንቅ ሥራዎቹን ለሕዝቦች ሁሉ ንገሩ።

25እግዚአብሔር ታላቅ ነው፤ ምስጋናውም ብዙ ነው፤

ከአማልክትም ሁሉ በላይ ሊፈራ የሚገባው ነው።

26የአሕዛብ ሁሉ አማልክት ጣዖታት ናቸው፤

እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሠራ።

27በፊቱ ክብርና ሞገስ አለ፤

ብርታትና ደስታም በማደሪያው ስፍራ።

28የአሕዛብ ወገኖች ለእግዚአብሔር ስጡ፤

ክብርና ኀይልን ለእግዚአብሔር አምጡ።

29ለስሙ የሚገባውን ክብር ለእግዚአብሔር ስጡ፤

መባ ይዛችሁ በፊቱ ቅረቡ፤

በቅድስናውም ክብር ለእግዚአብሔር16፥29 ወይም፣ ከክብሩ ጋር ለእግዚአብሔር ስገዱ።

30ምድር ሁሉ በፊቱ ትንቀጥቀጥ፤

ዓለም በጽኑ ተመሥርታለች፤ አትናወጥምም።

31ሰማያት ደስ ይበላቸው፤ ምድር ሐሤት ታድርግ፤

በአሕዛብም መካከል፤ “እግዚአብሔር ነገሠ!” ይበሉ።

32ባሕርና በውስጧ ያለው ሁሉ ይናወጥ፤

ሜዳዎችና በእርሷ ላይ ያሉ ሁሉ ሐሤት ያድርጉ።

33ያን ጊዜ የዱር ዛፎች በእግዚአብሔር ፊት ደስ ይላቸዋል፤

በደስታ ይዘምራሉ፤

በምድረ በዳ ላይ ሊፈርድ ይመጣልና።

34ቸር ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤

ፍቅሩም ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

35“አዳኛችን እግዚአብሔር ሆይ ታደገን፤

ለቅዱስ ስምህ ምስጋና እንድናቀርብ፣ በምስጋናህም እንድንከብር ሰብስበን፤

ከአሕዛብም መካከል ታደገን”

ብላችሁ ጩኹ።

36ከዘላለም እስከ ዘላለም፣

ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።

ከዚያም ሕዝቡ ሁሉ፣ “አሜን፤ እግዚአብሔር ይመስገን” አሉ።

37ዳዊትም ለእያንዳንዱ ቀን በተመደበው መሠረት፣ ዘወትር እንዲያገለግሉ አሳፍንና የሥራ ባልደረቦቹን በዚያው በእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ታቦት ፊት ተዋቸው። 38እንዲሁም ዖቤድኤዶምና ስድሳ ስምንቱ የሥራ ባልደረቦቹ አብረዋቸው እንዲያገለግሉ በዚያው ተዋቸው። የኤዶታም ልጅ ዖቤድኤዶምና ሖሳ የቅጥሩ በር ጠባቂዎች ሆኑ።

39ዳዊት ካህኑን ሳዶቅንና የሥራ ባልደረቦቹን ካህናት በገባዖን ከፍተኛ ቦታ ላይ በሚገኘው በእግዚአብሔር ድንኳን ተዋቸው፤ 40የተዋቸውም ለእስራኤል በተሰጠው ትእዛዝ መሠረት፣ በእግዚአብሔር ሕግ እንደ ተጻፈው ሁሉ፣ በመሠዊያው ላይ የሚቀርበውን የሚቃጠል መሥዋዕት ጧትና ማታ በየጊዜው እንዲያቀርቡ ነው። 41እንዲሁም “ፍቅሩ ለዘላለም ነውና” እያሉ ለእግዚአብሔር ምስጋና እንዲያቀርቡ ኤማንና ኤዶታም እንዲሁም ተመርጠውና ስማቸው ተመዝግቦ የተመደቡ ሌሎችም አብረዋቸው ነበሩ። 42ድምፀ መለከቱንና ጸናጽሉን ለማሰማት፣ ደግሞም መንፈሳዊ መዝሙር ሲዘመር ለሚጠቀሙባቸው ሌሎች መሣሪያዎች ኀላፊዎቹ ኤማንና ኤዶታም ነበሩ፤ የኤዶታምም ልጆች በሩን እንዲጠብቁ ተመድበው ነበር።

43ከዚያም ሕዝቡ ተነሣ፤ እያንዳንዱም ወደየቤቱ ሄደ። ዳዊትም ቤተ ሰቡን ለመባረክ ወደ ቤቱ ተመለሰ።