歷代志上 14 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

歷代志上 14:1-17

大衛的宮殿和家人

1泰爾希蘭差遣使者帶著香柏木、木匠和石匠去為大衛建造宮殿。 2那時,大衛知道耶和華已立他做以色列的王,並因自己以色列子民的緣故而使他國家興旺。

3大衛耶路撒冷又娶了多位妻子,生了許多兒女。 4他在耶路撒冷所生的孩子有沙姆亞朔罷拿單所羅門5益轄以利書亞以法列6挪迦尼斐雅非亞7以利沙瑪比利雅大以利法列

打敗非利士人

8非利士人聽說大衛已被膏立為以色列王,就全軍出動搜尋大衛大衛得知後,便出來迎敵。 9非利士人前來襲擊利乏音谷。 10大衛就求問上帝說:「我可以去迎戰非利士人嗎?你會把他們交在我手裡嗎?」耶和華說:「去吧,我必把他們交在你手裡。」

11於是,大衛前往巴力·毗拉心,擊敗了非利士人。他說:「上帝藉我的手擊潰敵人,如洪水沖垮堤岸。」所以,那地方叫巴力·毗拉心14·11 巴力·毗拉心」意思是「沖垮之主」。12非利士人在那裡丟棄了他們的神像,大衛命人把它們燒掉。 13非利士人又來襲擊那山谷, 14大衛又求問上帝,上帝對他說:「你不要正面出擊,要繞到他們後面,從桑林對面攻打他們。 15當你聽見桑樹梢上響起腳步聲時,就要進攻,因為那表示耶和華已在你前頭去攻擊非利士的軍隊了。」 16大衛遵命而行,打敗非利士人,從基遍一直殺到基色17於是,大衛名揚列國,耶和華使列國都懼怕他。

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 14:1-17

የዳዊት ቤትና ቤተ ሰቡ

14፥1-7 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 5፥11-161ዜና 3፥5-8

1በዚህ ጊዜ የጢሮስ ንጉሥ ኪራም ለዳዊት ቤተ መንግሥት እንዲሠሩ መልክተኞችን፣ ድንጋይ ጠራቢዎችንና ዐናጢዎችን ከዝግባ ዕንጨት ጋር ላከ። 2ዳዊትም እግዚአብሔር በእስራኤል ላይ አንግሦ እንዳጸናውና ስለ ሕዝቡም ስለ እስራኤል ሲል መንግሥቱን ከፍ ከፍ እንዳደረገለት አስተዋለ።

3ዳዊትም በኢየሩሳሌም ብዙ ሚስቶች አገባ፤ ከእነርሱም ወንዶችንና ሴቶች ልጆችን ወለደ። 4በዚያ ሳለ የወለዳቸው የልጆቹ ስም ይህ ነው፤ ሳሙስ፣ ሶባብ፣ ናታን፣ ሰሎሞን፣ 5ኢያቤሐር፣ ኤሊሱዔ፣ ኤሊፋላት፣ 6ኖጋ፣ ናፌቅ፣ ያፍያ፣ 7ኤሊሳማ፣ ኤሊዳሄ፣ ኤሊፋላት።

ዳዊት ፍልስጥኤማውያንን ድል አደረገ

14፥8-17 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 5፥17-25

8ዳዊት በእስራኤል ሁሉ ላይ ተቀብቶ መንገሡን ፍልስጥኤማውያን በሰሙ ጊዜ፣ እርሱን ፍለጋ በሙሉ ኀይላቸው ወጡ፤ ዳዊት ይህን ሰምቶ ስለ ነበር ሊገጥማቸው ወጣ። 9በዚህ ጊዜ ፍልስጥኤማውያን መጥተው የራፋይምን ሸለቆ ወረሩ። 10ስለዚህ ዳዊት፣ “ወጥቼ በፍልስጥኤማውያን ላይ አደጋ ልጣልን? አንተስ በእጄ አሳልፈህ ትሰጣቸዋለህን?” ሲል እግዚአብሔርን ጠየቀ።

እግዚአብሔርም፣ “አዎን ውጣ! በእጅህ አሳልፌ እሰጣቸዋለሁ” ብሎ መለሰለት።

11ስለዚህ ዳዊትና ሰዎቹ ወደ በኣልፐራሲም ወጡ፤ በዚያም ድል አደረጋቸው። ዳዊትም፣ “ውሃ ነድሎ እንደሚወጣ ሁሉ እግዚአብሔርም ጠላቶቼን በእጄ አፈረሳቸው” አለ፤ ከዚህም የተነሣ ያን ቦታ “በኣልፐራሲም” ብለው ሰየሙት። 12ፍልስጥኤማውያን አማልክታቸውን በዚያው ጥለዋቸው ስለ ነበር፣ ዳዊት በእሳት እንዲያቃጥሏቸው አዘዘ።

13ፍልስጥኤማውያን ሸለቆውን እንደ ገና ወረሩ፤ 14ዳዊትም እንደ ገና እግዚአብሔርን ጠየቀ። እግዚአብሔርም እንዲህ ሲል መለሰለት “ዙሪያውን ከብበህ በሾላው ዛፍ ፊት ለፊት አደጋ ጣልባቸው እንጂ በቀጥታ ወደ ላይ አትውጣ፤ 15በሾላው ዐናት ላይ የሰልፍ ድምፅ ስትሰማ ወዲያውኑ ለጦርነት ውጣ፤ ይህም የፍልስጥኤማውያንን ሰራዊት ለመምታት እግዚአብሔር በፊትህ ወጥቷል ማለት ነውና።” 16ስለዚህ ዳዊት እግዚአብሔር እንዳለው አደረገ፤ ከገባዖን ጀምሮ እስከ ጌዝር ድረስ ፍልስጥኤማውያንን መቷቸው።

17ከዚህም የተነሣ የዳዊት ዝና በየአገሩ ሁሉ ተሰማ፤ እግዚአብሔርም መንግሥታት ሁሉ እንዲፈሩት አደረገ።