撒迦利亞書 9 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

撒迦利亞書 9:1-17

審判鄰國

1以色列各支派一樣,

世人的眼目都仰望耶和華。9·1 與以色列各支派一樣,世人的眼目都仰望耶和華」或譯「耶和華鑒察以色列各支派,也鑒察所有的世人」。

以下是耶和華的啟示:

祂的懲罰必臨到哈得拉

臨到大馬士革

2以及與大馬士革比鄰的哈馬

極其聰明的泰爾西頓也無法倖免。

3泰爾為自己建造堡壘,

堆積的銀子多如塵土,

金子多如街上的泥土。

4然而,看啊,主必奪去她的一切,

摧毀她海上的權勢,

使她被火吞噬。

5亞實基倫見狀必陷入恐懼,

迦薩見狀必充滿痛苦,

以革倫見狀必希望破滅。

迦薩必失去君王,

亞實基倫必荒無人煙。

6混雜的種族必佔領亞實突

9·6 」指耶和華,下同。必剷除非利士人的驕傲。

7我必除去他們口中帶血的肉和齒間的可憎之物。

餘下的人必歸屬我9·7 」希伯來文作「我們的上帝」。

成為猶大的一族,

以革倫人必像耶布斯人一樣歸屬我。

8我必在我家四周安營,

不容敵人入侵,

再也不容外人來欺壓我的子民,

因為現在我親自看顧他們。

要來的君王

9錫安城啊,要充滿喜樂!

耶路撒冷城啊,要歡呼!

看啊,你的王到你這裡來了!

祂是公義、得勝的王,

謙卑地騎著驢,

騎著一頭驢駒。

10我必剷除以法蓮的戰車,

剷除耶路撒冷的戰馬,

戰弓必被折斷。

祂必向列國宣告和平,

祂必統治四海之疆,

幼發拉底河直到地極。

11錫安啊,因為我用血跟你立了約,

我必將你中間被擄的人從無水之坑釋放出來。

12有盼望的被擄者啊,回到你們的堡壘吧。

今日我宣佈,我必加倍地補償你們。

13我必把猶大當弓拉開,

以法蓮當箭搭上,

使錫安的眾子如勇士之劍,

去攻打希臘的眾子。

14耶和華必在他們上面顯現,

祂的箭如閃電射出。

主耶和華必吹響號角,

乘南方的暴風而來。

15萬軍之耶和華必保護他們,

他們必用彈石消滅、征服敵人,

飲血呐喊,猶如醉酒,

像獻祭用的碗盛滿了血,

又像祭壇的四角淌滿了血。

16到那天,他們的上帝耶和華必拯救他們,

視他們為一群祂的子民。

他們必如王冠上的寶石閃耀在祂的土地上。

17那將是何等的奇妙,何等的美好!

五穀必滋養少男,

新酒必滋養少女。

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 9:1-17

በእስራኤል ጠላቶች ላይ የተወሰነ ፍርድ

1የእግዚአብሔር ቃል ንግር በሴድራክ ምድር ላይ ይወርድበታል፤

በደማስቆም ላይ ያርፍበታል፤

የሰዎችና የእስራኤል ነገዶች ሁሉ ዐይን፣

በእግዚአብሔር ላይ9፥1 ወይም ደማስቆ የእግዚአብሔር ዐይን በሰው ሁሉ ላይ ያያልና በእስራኤል ነገዶች ላይ እንደ ሆነው። ዐርፏልና።

2ደግሞም በአዋሳኟ በሐማት፣

ጥበበኞች ቢሆኑም እንኳ በጢሮስና በሲዶና ላይ ያርፍባቸዋል።

3ጢሮስ ለራሷ ምሽግ ሠርታለች፤

ብሩን እንደ ዐፈር

ወርቁንም እንደ መንገድ ላይ ትቢያ ቈልላለች።

4ጌታ ግን ሀብቷን ይወስዳል፤

በባሕር ያላትንም ኀይል ይደምስሳል፤

እርሷም በእሳት ፈጽማ ትጠፋለች።

5አስቀሎና አይታ ትርዳለች፤

ጋዛ በሥቃይ ትቃትታለች፤

አቃሮናም እንደዚሁ ትሠቃያለች፤ ተስፋዋ ይመነምናልና።

ጋዛ ንጉሥዋን ታጣለች፤

አስቀሎናም ባድማ ትሆናለች።

6ድብልቅ ሕዝቦች አዛጦንን ይይዛሉ፤

የፍልስጥኤማውያንንም ትምክሕት እቈርጣለሁ።

7ደሙን ከአፋቸው፣

የተከለከለውንም ምግብ ከመንጋጋቸው አወጣለሁ።

የተረፉት ለአምላካችን ይሆናሉ፤

በይሁዳም አለቆች ይሆናሉ፤

አቃሮንም እንደ ኢያቡሳዊ ይሆናል።

8እኔ ግን ቤቴን

ከዘራፊ ኀይሎች እጠብቃለሁ፤

ጨቋኝ ከእንግዲህ ሕዝቤን አይወርስም፤

አሁን ነቅቼ እጠብቃለሁና።

የጽዮን ንጉሥ መምጣት

9አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፤ እጅግ ደስ ይበልሽ፤

አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፤ እልል በዪ፤

እነሆ፤ ጻድቁና አዳኙ ንጉሥሽ9፥9 ወይም ንጉሥ ማለት ይሆናል

ትሑት ሆኖ፣ በአህያ ላይ ተቀምጦ፣

በአህያ ግልገል፣ በውርንጫዪቱ ላይ ሆኖ

ወደ አንቺ ይመጣል።

10ሠረገሎችን ከኤፍሬም፣

የጦር ፈረሶችን ከኢየሩሳሌም እወስዳለሁ፤

የጦርነቱም ቀስት ይሰበራል፤

ሰላምን ለአሕዛብ ያውጃል፤

ግዛቱም ከባሕር እስከ ባሕር፣

ከወንዙም9፥10 ኤፍራጥስም ነው እስከ ምድር9፥10 ወይም፣ ምድር ዳርቻ ማለት ነው። ዳር ድረስ ይዘረጋል።

11ለአንቺ ደግሞ፣ ከአንቺ ጋር ከገባሁት የደም ቃል ኪዳን የተነሣ፣

እስረኞችሽን ውሃ ከሌለበት ጕድጓድ ነጻ እለቅቃቸዋለሁ።

12እናንት በተስፋ የምትኖሩ እስረኞች፤ ወደ ምሽጎቻችሁ ተመለሱ፤

አሁንም ቢሆን ሁለት ዕጥፍ አድርጌ እንደምመልስላችሁ እናገራለሁ።

13ቀስቴን እንደ ገተርሁ፣ ይሁዳን እገትረዋለሁ፤

ኤፍሬምንም ፍላጻ አደርገዋለሁ።

ጽዮን ሆይ፤ ልጆችሽን አስነሣለሁ፤

ግሪክ ሆይ፤ በአንቺ ልጆች ላይ ይነሣሉ፤

እንደ ተዋጊ ሰይፍም አደርግሻለሁ።

እግዚአብሔር ይገለጣል

14እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ ይገለጣል፤

ፍላጻውም እንደ መብረቅ ይወጣል፤

ጌታ እግዚአብሔር መለከት ይነፋል፤

በደቡብም ዐውሎ ንፋስ ውስጥ ይጓዛል፤

15እግዚአብሔር ጸባኦትም ይከልላቸዋል፤

ጠላቶቻቸውን ይደመስሳሉ፤

በድንጋይ ወንጭፍም ያሸንፋሉ፤

ይጠጣሉ፤ በወይን ጠጅ እንደ ሰከረ ሰው ይጮኻሉ፤

የመሠዊያውን ማእዘኖች ለመርጨት፣

እንደ ተዘጋጀ ዕቃ9፥15 ወይም ጽዋ፣ እነርሱም እንደዚሁ ተሞልተዋል።

16ሕዝቡን የራሱ መንጋ አድርጎ

በዚያ ቀን አምላካቸው እግዚአብሔር ያድናቸዋል።

በአክሊል ላይ እንዳለ ዕንቍ፣

በገዛ ምድሩ ላይ ያብለጨልጫሉ።

17እንዴት ውብና አስደናቂ ይሆናሉ፤

እህል ጕልማሶችን፣

አዲስ የወይን ጠጅም ቈነጃጅትን ያሳምራል።