撒迦利亞書 7 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

撒迦利亞書 7:1-14

呼籲公義和憐憫

1大流士王四年九月,即基斯流月四日,耶和華的話傳給了撒迦利亞2那時,伯特利人差遣沙利色利堅米勒及其隨從去向耶和華求恩。 3他們問萬軍之耶和華殿裡的祭司和先知:「我們還要照多年的慣例在五月哀傷、禁食嗎?」

4萬軍之耶和華的話傳給了我,說: 5「你要對境內的民眾和祭司說,『七十年來,你們在五月和七月禁食、哀傷,難道真的是為了我嗎? 6你們吃喝,難道不是為自己吃、為自己喝嗎? 7這些不是耶和華藉從前的先知所宣告的嗎?當時耶路撒冷和周圍的城邑人口興盛、繁榮,南地和丘陵都有人居住。』」

8耶和華的話又傳給了撒迦利亞,說: 9「萬軍之耶和華曾對你們的祖先說,『要秉公行義,彼此以慈愛和憐憫相待。 10不可欺壓寡婦、孤兒、寄居者和窮人,不可設陰謀彼此相害。』 11他們卻不理會,背過身去,充耳不聞, 12心如鐵石,不遵從律法,也不遵從萬軍之耶和華藉著祂的靈指示從前的先知所說的話。因此,萬軍之耶和華非常憤怒。 13祂說,『我曾呼喚他們,他們不聽;將來他們呼求我,我也不聽。 14我要用旋風把他們吹散到陌生的萬國中,使他們的土地荒涼、杳無人跡,因為他們使美好的土地一片荒涼。』」

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 7:1-14

ፍትሕና ምሕረት የተወደደ ነው

1ዳርዮስ በነገሠ በአራተኛው ዓመት፣ ካሴሉ በተባለው በዘጠነኛው ወር፣ በአራተኛው ቀን የእግዚአብሔር ቃል ወደ ዘካርያስ እንዲህ ሲል መጣ፤ 2የቤቴል ሰዎች እግዚአብሔርን ለመለመን ሳራሳርንና ሬጌሜሌክን አብረዋቸው ከነበሩት ሰዎች ጋር ላኩ፤ 3እነርሱም የእግዚአብሔር ጸባኦት ቤት ካህናትና ነቢያት፣ “ብዙ ዓመት እንዳደረግሁት፣ በአምስተኛው ወር ማዘንና መጾም ይገባኛልን?” ብለው ጠየቁ።

4ከዚያም የእግዚአብሔር ጸባኦት ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 5“የምድሩን ሕዝብ ሁሉና ካህናቱን እንዲህ በላቸው፤ ‘ባለፉት ሰባ ዓመታት በአምስተኛውና በሰባተኛው ወር የጾማችሁትና ያዘናችሁት በርግጥ ለእኔ ነበርን? 6ትበሉና ትጠጡ የነበረውስ ለራሳችሁ አይደለምን? 7ኢየሩሳሌምና በዙሪያዋ ያሉ ከተሞች በሰላምና በብልጽግና ላይ ሳሉ፣ የደቡብና የምዕራብ ኰረብቶች ግርጌ የሰው መኖሪያም በነበሩበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር በቀደሙት ነቢያት የተናገረው ቃል ይህ አልነበረምን?’ ”

8የእግዚአብሔር ቃል እንደ ገና ወደ ዘካርያስ እንዲህ ሲል መጣ፤ 9እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤ ‘እውነተኛ ፍትሕ አስፍኑ፣ እርስ በርሳችሁ ምሕረትና ርኅራኄን አድርጉ፤ 10መበለቲቱን ወይም ድኻ ዐደጉን፣ መጻተኛውን ወይም ድኻውን አታስጨንቁ፤ በልባችሁም አንዳችሁ በአንዳችሁ ላይ ክፉ አታስቡ።’

11“እነርሱ ግን መስማት አልፈለጉም፤ በእልኸኝነት ጀርባቸውን አዞሩ፤ ጆሯቸውንም ደፈኑ። 12ልባቸውን እንደ ባልጩት አጠነከሩ፤ እግዚአብሔር ጸባኦት በቀደሙት ነቢያት በኩል በመንፈሱ የላከውን ቃል ወይም ሕግ አልሰሙም፤ ስለዚህ እግዚአብሔር ጸባኦት እጅግ ተቈጣ።

13“ ‘ስጠራቸው አልሰሙም፤ ስለዚህ ሲጠሩኝ አልሰማም’ ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት። 14‘በማያውቋቸው በባዕዳን አሕዛብ መካከል በዐውሎ ነፋስ በተንኋቸው፤ ከእነርሱ በኋላ ማንም እስከማይመጣባትና እስከማይሄድባት ድረስ ምድሪቱ ባድማ ሆነች፤ መልካሚቱን ምድር ባድማ ያደረጓት በዚህ ሁኔታ ነው።’ ”