撒迦利亞書 12 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

撒迦利亞書 12:1-14

耶路撒冷必蒙拯救

1以下是耶和華關於以色列的啟示。

鋪展穹蒼、奠立大地的根基、塑造人靈魂的耶和華說: 2「看啊,我要使耶路撒冷成為令周圍萬民昏醉的酒杯。耶路撒冷被圍困時,猶大也必受困。 3到那天,當地上的列國聚集起來攻擊耶路撒冷的時候,我要使耶路撒冷成為一塊沉重的石頭。凡試圖舉起它的,必傷自己。 4到那天,我要使所有的戰馬驚恐,使馬上的騎士癲狂。我必看顧猶大家,使列邦的馬匹瞎眼。這是耶和華說的。 5那時,猶大的族長必心裡說,『耶路撒冷的居民從他們的上帝——萬軍之耶和華那裡得到了力量。』

6「到那天,我必使猶大的族長像木柴中的火盆,像禾捆中的火把,吞噬左右四圍的列邦,但耶路撒冷人必仍在原處——耶路撒冷安居。

7「耶和華必首先拯救猶大的帳篷,免得大衛家和耶路撒冷居民的榮耀超過猶大8到那天,耶和華必保護耶路撒冷的居民,使他們當中最軟弱的像大衛一樣剛強,使大衛家像上帝一樣,像耶和華的天使一樣帶領他們。 9到那天,我必毀滅前來攻擊耶路撒冷的列國。

10「我必將施恩和禱告的靈澆灌在大衛家和耶路撒冷的居民身上。他們必仰望我——他們所刺的那位,如喪獨子一般為祂哀傷,如喪長子一般為祂痛哭。 11到那天,耶路撒冷必一片哀聲,猶如米吉多平原的哈達臨門的哀聲。 12境內家家戶戶都必哀哭。大衛家的男子在一處,女子在一處;拿單家的男子在一處,女子在一處; 13利未家的男子在一處,女子在一處;示每家的男子在一處,女子在一處。 14其餘各家也都哀哭,男女分開。

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 12:1-14

የኢየሩሳሌም ጠላቶች እንደሚደመሰሱ የተነገረ ንግር

1ስለ እስራኤል የተነገረው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤ ሰማያትን የዘረጋ፣ ምድርን የመሠረተ የሰውንም መንፈስ በውስጡ የሠራ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ 2“ኢየሩሳሌምን በዙሪያዋ ላሉት ሕዝቦች ሁሉ የሚያንገደግድ ጽዋ አደርጋታለሁ፤ ይሁዳም እንደ ኢየሩሳሌም ሁሉ ትከበባለች። 3የምድር አሕዛብ ሁሉ በእርሷ ላይ በሚሰበሰቡበት በዚያ ቀን፣ ኢየሩሳሌምን ለአሕዛብ ሁሉ የማይነቃነቅ ዐለት አደርጋታለሁ፤ ለማነቃነቅ የሚሞክሩ ሁሉ ራሳቸውን ይጐዳሉ። 4በዚያን ቀን እያንዳንዱን ፈረስ በድንጋጤ፣ የተቀመጡባቸውንም ሰዎች እብደት እመታለሁ” ይላል እግዚአብሔር። “የይሁዳን ቤት በዐይኔ እጠብቃለሁ፤ ነገር ግን የአሕዛብን ፈረሶች ሁሉ አሳውራለሁ። 5የይሁዳ መሪዎች በልባቸው፣ ‘የኢየሩሳሌም ሕዝቦች ብርቱ ናቸው፤ አምላካቸው እግዚአብሔር ጸባኦት ነውና’ ይላሉ።

6“በዚያ ቀን የይሁዳን መሪዎች በዕንጨት ክምር ውስጥ እንዳለ የእሳት ምድጃ፣ በነዶም መካከል እንዳለ የፋና ነበልባል አደርጋቸዋለሁ፤ በግራና በቀኝ ዙሪያውን ያሉትን ሕዝቦች ይበላሉ፤ ኢየሩሳሌም ግን ከስፍራዋ ንቅንቅ አትልም።

7“የዳዊት ቤትና የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ክብር ከይሁዳ ክብር እንዳይበልጥ እግዚአብሔር በመጀመሪያ የይሁዳን መኖሪያዎች ያድናል። 8ከመካከላቸው እጅግ ደካማ የሆነው እንደ ዳዊት፣ የዳዊት ቤትም ፊት ፊታቸው እንደሚሄድ እንደ እግዚአብሔር መልአክ፣ እንደ አምላክ ይሆንላቸው ዘንድ በኢየሩሳሌም የሚኖሩትን እግዚአብሔር ይከልላቸዋል። 9በዚያ ቀን ኢየሩሳሌምን በወጓት አሕዛብ ሁሉ ላይ እወጣለሁ።

ስለ ወጉት የተደረገ ሐዘን

10“በዳዊት ቤትና በኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ላይ የርኅራኄና የልመና መንፈስ አፈስሳለሁ፤ ወደ ወጉኝ ወደ12፥10 ወይም ለእኔ ሊሆን ይችላል። እኔም ይመለከታሉ፤ እነርሱም ለአንድያ ልጅ እንደሚለቀስ ያለቅሱለታል፤ ለበኵር ልጅ ምርር ተብሎ እንደሚለቀስም አምርረው ያለቅሱለታል።” 11በዚያ ቀን በመጊዶን ሜዳ ለሐዳድሪሞን እንደ ተለቀሰ ሁሉ በኢየሩሳሌም የሚለቀሰውም እንደዚሁ ታላቅ ልቅሶ ይሆናል። 12ምድሪቱ ታለቅሳለች፤ የየነገዱ ወንዶች ለየራሳቸው ያለቅሳሉ፤ ሚስቶቻቸውም ለየራሳቸው ያለቅሳሉ፤ በዚህም ዐይነት የዳዊት ቤት ነገድ ወንዶች ከነሚስቶቻቸው፣ የናታን ቤት ነገድ ወንዶች ከነሚስቶቻቸው፣ 13የሌዊ ቤት ነገድ ወንዶች ከነሚስቶቻቸው፣ የሰሜኢ ቤት ነገድ ወንዶች ከነሚስቶቻቸው፣ 14የቀሩትም ነገዶች ወንዶች ሁሉ ከነሚስቶቻቸው ያለቅሳሉ።