提摩太前書 6 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

提摩太前書 6:1-21

1作奴僕的要全心尊重自己的主人,免得上帝的名和我們的教導被人褻瀆。 2若主人是基督徒,作奴僕的不可因為同是信徒就不尊敬自己的主人,反而要更好地服侍他,因為這些接受服侍的人是信徒,是主所愛的。你要教導這些事並勉勵眾人。

異端與貪財

3如果有人傳的教義不符合我們主耶穌基督純正的道和敬虔的教導, 4他就是狂妄自大、一無所知。這種人專好問難,爭辯字句,結果引起嫉妒、紛爭、毀謗和猜忌, 5使那些思想敗壞、失去真理的人爭論不休,甚至把敬虔當作生財之道。 6其實敬虔和知足才是真正的財富, 7因為我們空手來到世上,也要空手離開。 8只要有吃有穿,就該知足。 9那些渴望發財的人卻陷入誘惑、網羅和許多愚蠢有害的慾望中,以致落入敗壞和滅亡中。 10貪財是萬惡之根,有人因為貪財就離棄了信仰,結果飽嚐種種錐心般的痛苦。

保羅對提摩太的囑咐

11但你這屬上帝的人要遠避這些事,要追求公義、敬虔、信心、愛心、忍耐和溫柔, 12要為真道打美好的仗,要持定永生。你是為永生蒙召的,並在許多見證人面前做過美好的見證。 13在賜萬物生命的上帝面前,也在向本丟·彼拉多做過美好見證的基督耶穌面前,我囑咐你: 14要遵守這命令,做純潔無瑕、無可指責的人,一直到我們的主耶穌基督再來。 15到了時候,配得稱頌、獨有權能的萬王之王、萬主之主要使基督顯現。 16上帝是獨一不朽的,住在人不能接近的光中,從來沒有人見過祂,也沒有人能夠看見祂。願尊貴和永遠的權柄都歸給祂。阿們!

17你要勸誡那些今世富足的人不要高傲,也不要冀望於靠不住的錢財,要信靠將萬物厚賜給我們享用的上帝。 18你要勸他們多多行善、慷慨施捨、樂意助人。 19這樣,他們可以為自己的將來奠定美好的基礎,以便持守真正的生命。

20提摩太啊,你要持守所託付給你的,避開世俗的空談和那些違背真理、似是而非的學問。 21有些自稱有這種學問的人已經偏離了信仰。

願恩典與你們同在!

New Amharic Standard Version

1 ጢሞቴዎስ 6:1-21

1የእግዚአብሔር ስምና ትምህርቱም እንዳይሰደቡ፣ በባርነት ቀንበር ሥር ያሉ ሁሉ፣ ጌቶቻቸው ሙሉ ክብር እንደሚገባቸው አድርገው ይቍጠሩ። 2የሚያምኑ ጌቶች ያሏቸውም፣ ወንድሞች ስለ ሆኑ የሚገባቸውን ክብር አይንፈጓቸው፤ ይልቁንም በአገልግሎታቸው የሚጠቀሙ አማኞችና ወዳጆቻቸው ስለ ሆኑ የበለጠ ሊያገለግሏቸው ይገባል። እነዚህን ነገሮች አስተምር፤ ምከርም።

የገንዘብ ፍቅር

3ማንም የሐሰት ትምህርት ቢያስተምር፣ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጤናማ ቃልና እውነተኛ መንፈሳዊነትን ከሚያጐለብት ትምህርት ጋር የማይስማማ ቢሆን፣ 4ያ ሰው በትዕቢት ተወጥሯል፤ አንዳችም አያስተውልም። ስለ ቃላት ለመከራከርና ለመጣላት ክፉ ጕጕት አለው፤ እነዚህም ቅናትን፣ ጥልን፣ ስድብን፣ መጥፎ ጥርጣሬን ያስከትላሉ፤ 5እውነትን በተቀሙና መንፈሳዊው ነገር ትርፍ ማግኛ በሚመስላቸው፣ አእምሮ በጐደላቸው ሰዎችም መካከል የማያባራ ንትርክ ያመጣሉ።

6ነገር ግን እውነተኛ መንፈሳዊነት ባለን ነገር ከመርካት ጋር ትልቅ ትርፍ ነው። 7ምክንያቱም ወደ ዓለም ያመጣነው ምንም ነገር የለም፤ ምንም ነገር ይዘን መሄድም አንችልም። 8ነገር ግን ምግብና ልብስ ካለን፣ ያ ይበቃናል። 9ባለጠጋ ለመሆን የሚፈልጉ ግን ወደ ፈተናና ወደ ወጥመድ፣ እንዲሁም ሰዎችን ወደ መፍረስና ወደ ጥፋት ወደሚያዘቅጠው ወደ ብዙ ከንቱና ክፉ ምኞት ይወድቃሉ። 10ምክንያቱም የገንዘብ ፍቅር የክፋት ሁሉ ሥር ነው። አንዳንዶች ባለጠጋ ለመሆን ካላቸው ጕጕት የተነሣ ከእምነት መንገድ ስተው ሄደዋል፤ ራሳቸውንም በብዙ ሥቃይ ወግተዋል።

ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ የሰጠው ዐደራ

11የእግዚአብሔር ሰው ሆይ፤ አንተ ግን ከዚህ ሁሉ ሽሽ፤ ጽድቅን፣ እውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወትን፣ እምነትን፣ ፍቅርን፣ ትዕግሥትንና ገርነትን ተከታተል። 12መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል፤ በብዙ ምስክሮች ፊት በመልካም መታመን የመሰከርህለትንና የተጠራህበትን የዘላለም ሕይወት አጥብቀህ ያዝ። 13ለሁሉም ሕይወትን በሚሰጥ በእግዚአብሔር ዘንድ እንዲሁም በጳንጥዮስ ጲላጦስ ፊት እውነትን በመሰከረ በክርስቶስ ኢየሱስ ፊት ዐደራ የምልህ፣ 14ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስኪገለጥ ድረስ ይህን ትእዛዝ ያለ ዕድፍና ያለ ነቀፋ ሆነህ እንድትጠብቅ ነው፤ 15ያም መገለጥ፣ የተባረከውና ብቻውን ገዥ የሆነው የነገሥታት ንጉሥ፣ የጌቶችም ጌታ እግዚአብሔር በራሱ ጊዜ የሚያሳየው ነው፤ 16እርሱ ብቻ ኢመዋቲ ነው፤ ሊቀረብ በማይቻል ብርሃን ውስጥ ይኖራል፤ እርሱን ያየ ማንም የለም፤ ሊያየውም የሚችል የለም። ለእርሱ ክብርና ኀይል ከዘላለም እስከ ዘላለም ይሁን፤ አሜን።

17በዚህ ዓለም ባለጠጎች የሆኑት እንዳይታበዩ፣ ደስም እንዲለን ሁሉን ነገር አትረፍርፎ በሚሰጠን በእግዚአብሔር እንጂ አስተማማኝነት በሌለው በሀብት ላይ ተስፋ እንዳያደርጉ እዘዛቸው። 18መልካም እንዲሠሩ፣ ቸሮችና ለማካፈል ፈቃደኞች የሆኑ እንዲሆኑ እዘዛቸው። 19በዚህ ዐይነት እውነተኛ የሆነውን ሕይወት ያገኙ ዘንድ፣ ለሚመጣው ዘመን ጽኑ መሠረት የሚሆን ሀብት ለራሳቸው ያከማቻሉ።

20ጢሞቴዎስ ሆይ፤ በዐደራ የተቀበልኸውን ሁሉ ጠብቅ፤ እግዚአብሔርን ከማያስከብር ከከንቱ ልፍለፋና ለተቃውሞ በውሸት ዕውቀት ከተባለ ፍልስፍና ራቅ፤ 21የዚህ ዐይነት ዕውቀት አለን ሲሉ የነበሩ አንዳንዶች ይህን በማድረጋቸው ከእምነት መንገድ ስተው ሄደዋል።

ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።