啟示錄 1 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

啟示錄 1:1-20

1以下是上帝賜給耶穌基督的啟示,讓祂把將來要發生的事指示祂的眾奴僕。因此,祂差遣天使告訴祂的奴僕約翰2約翰便為自己所看見的一切——上帝的道和耶穌基督做見證。 3那位宣讀這預言的人和那些聽見並遵守其中內容的人有福了,因為日期近了。

問候七教會

4-5約翰寫信給你們亞細亞的七間教會。願昔在、今在、以後永在的上帝,祂寶座前的七靈1·4-5 七靈」指的就是聖靈,數字七代表完全,不是說有七個靈。和耶穌基督賜給你們恩典和平安。耶穌基督是忠心的見證人,是首先從死裡復活的,是世上君王的首領。祂愛我們,用自己的血救我們脫離罪惡, 6使我們成為祭司的國度1·6 成為祭司的國度」或譯「成為國度,做祭司」。來事奉祂的父上帝。願祂得到一切榮耀和權柄,一直到永永遠遠。阿們!

7看啊!祂要駕雲降臨,世人都要看見祂,包括曾經刺祂的人。地上的萬族都必因祂而哀哭。這事必定實現。阿們!

8主上帝說:「我是阿拉法,我是俄梅加1·8 阿拉法」和「俄梅加」分別是希臘文第一個和最後一個字母,故此句意即「我是始,我是終」。,我是昔在、今在、以後永在的全能者。」

基督的顯現

9約翰是你們的弟兄,在耶穌裡和你們患難與共、同享國度、一起忍耐。我因傳揚上帝的道、為主耶穌做見證而到了拔摩海島上。 10主日,我被聖靈感動,聽見身後有號角般響亮的聲音說: 11「把你所看見的寫在書上,然後送給以弗所士每拿別迦摩推雅推喇撒狄非拉鐵非老底嘉七間教會。」

12我轉身看究竟是誰在對我說話,我看見七個金燈臺, 13有一位好像人子耶穌的站在這些燈臺中間。祂長袍垂腳,金帶圍胸, 14頭與髮白如羊毛、潔白如雪,眼睛像火焰, 15雙腳像爐中冶煉過的銅一樣光亮,聲音如同洪濤之聲。 16祂右手拿著七顆星,口中吐出一把兩刃的利劍,面貌如烈日放光。

17我一看見祂,便仆倒在祂腳前,像死了一樣。祂把右手按在我身上,說:「不要害怕!我是首先的,我是末後的, 18我是永活者。我曾經死過,但看啊,我永永遠遠活著。我掌握死亡和陰間的鑰匙。 19所以,你要將所看見的一切——現在和將來要發生的事都記錄下來。 20你所看見在我右手中的七顆星和七個金燈臺的奧祕是,七顆星代表七間教會的天使1·20 天使」或譯「信使」或「使者」,下同,可能指教會的守護天使,或者是教會的領袖。,七個燈臺代表七間教會。

New Amharic Standard Version

ራእይ 1:1-20

1ቶሎ መሆን የሚገባውን ነገር ለአገልጋዮቹ እንዲያሳይ፣ እግዚአብሔር ለእርሱ የሰጠው የኢየሱስ ክርስቶስ ራእይ ይህ ነው፤ ኢየሱስም መልአኩን ልኮ ለአገልጋዩ ለዮሐንስ ገለጠለት፤ 2እርሱም ስለ እግዚአብሔር ቃልና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ምስክርነት ያየውን ሁሉ መሰከረ። 3ዘመኑ ቀርቧል፤ እንግዲህ ይህን የትንቢት ቃል የሚያነብብ ብፁዕ ነው፤ የሚሰሙትና የተጻፈውንም የሚጠብቁ ብፁዓን ናቸው።

ሰላምታና ውዳሴ

4ከዮሐንስ፤

በእስያ አውራጃ ለሚገኙ ለሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት፤

ካለው፣ ከነበረውና ከሚመጣው፣ በዙፋኑም ፊት ካሉት ከሰባቱ መናፍስት፣1፥4 ወይም ሰባት ዕጥፍ መንፈስ 5እንዲሁም ታማኝ ምስክር፣ ከሙታን በኵርና የምድር ነገሥታት ገዥ ከሆነው ከኢየሱስ ክርስቶስም ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።

ለወደደንና ከኀጢአታችንም በደሙ ነጻ ላወጣን፣ 6አምላኩንና አባቱን እንድናገለግልም መንግሥትና ካህናት ላደረገን፣ ለእርሱ ክብርና ኀይል ከዘላለም እስከ ዘላለም ይሁን! አሜን።

7እነሆ፤ በደመና ይመጣል፤

የወጉት እንኳ ሳይቀሩ፣

ዐይን ሁሉ ያየዋል፤

የምድርም ሕዝቦች ሁሉ ከእርሱ የተነሣ ዋይ ዋይ ይላሉ።

አዎ! ይህ ሁሉ ይሆናል፤ አሜን።

8“ያለውና የነበረው፣ የሚመጣውም፣ ሁሉን ቻይ ጌታ አምላክ፣ አልፋና ዖሜጋ እኔ ነኝ” ይላል።

የሰውን ልጅ የሚመስለው

9እኔ ወንድማችሁ ዮሐንስ፣ ከእናንተ ጋር አብሬ በኢየሱስ መከራውንና መንግሥቱን፣ ትዕግሥቱንም ተካፋይ የሆንሁ፣ ስለ እግዚአብሔር ቃልና ስለ ኢየሱስ ምስክርነት ፍጥሞ በምትባል ደሴት ነበርሁ። 10በጌታ ቀን በመንፈስ ነበርሁ፤ የመለከትን ድምፅ የሚመስል ታላቅ ድምፅ ከበስተ ኋላዬ ሰማሁ፤ 11ድምፁም፣ “የምታየውን በጥቅልል መጽሐፍ ጽፈህ በኤፌሶን፣ በሰምርኔስ፣ በጴርጋሞን፣ በትያጥሮን፣ በሰርዴስ፣ በፊላድልፍያና በሎዶቅያ ወደሚገኙት ወደ ሰባቱ የእስያ አብያተ ክርስቲያናት ላክ” አለ።

12እኔም የሚናገረኝን ድምፅ ለማየት ዞር አልሁ፤ ዞር ባልሁም ጊዜ ሰባት የወርቅ መቅረዞችን አየሁ፤ 13በመቅረዞቹም መካከል “የሰው ልጅ የሚመስል” አየሁ፤ እርሱም እስከ እግሩ የሚደርስ መጐናጸፊያ የለበሰ፣ ደረቱንም በወርቅ መታጠቂያ የታጠቀ ነበር። 14ራሱና ጠጕሩም እንደ ነጭ የበግ ጠጕር፣ እንደ በረዶም ነጭ ነበሩ፤ ዐይኖቹም የእሳት ነበልባል ይመስሉ ነበር። 15እግሮቹ በእቶን እሳት የጋለ ናስ ይመስሉ ነበር፤ ድምፁም እንደ ብዙ ወራጅ ውሃ ድምፅ ነበረ። 16በቀኝ እጁ ሰባት ከዋክብት ይዞ ነበር፤ ከአፉም በሁለት በኩል የተሳለ ሰይፍ ይወጣ ነበር፤ ፊቱም በሙሉ ድምቀቱ እንደሚያበራ ፀሓይ ነበረ።

17ባየሁት ጊዜ እንደ ሞተ ሰው ሆኜ በእግሩ ሥር ወደቅሁ። እርሱም ቀኝ እጁን በላዬ ጭኖ እንዲህ አለኝ፤ “አትፍራ፤ የመጀመሪያውም የመጨረሻውም እኔ ነኝ፤ 18እኔ ሕያው ነኝ፤ ሞቼ ነበር፤ እነሆ፤ አሁን ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፤ የሞትና የሲኦል መክፈቻም በእጄ ነው።

19“ስለዚህ ያየኸውን፣ አሁን ያለውንና በኋላም የሚሆነውን ጻፍ። 20በቀኝ እጄ ያየሃቸው የሰባቱ ከዋክብትና የሰባቱ የወርቅ መቅረዞች ምስጢር ይህ ነው፤ ሰባቱ ከዋክብት የሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት መላእክት1፥20 ወይም መልእክተኞች ናቸው፤ ሰባቱ መቅረዞች ደግሞ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት ናቸው።