創世記 4 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

創世記 4:1-26

該隱和亞伯

1亞當和他妻子夏娃同房,夏娃便懷孕,生了該隱。她說:「耶和華讓我得了一個男孩。」 2後來,夏娃又生了該隱的弟弟亞伯。長大後,亞伯做了牧羊人,該隱做了農夫。

3到了收成的時候,該隱把地裡的出產當祭物獻給耶和華, 4亞伯也把羊群中頭生的羊及其最肥美的部分獻給耶和華。耶和華悅納亞伯和他的祭物, 5卻不悅納該隱和他的祭物。該隱便非常惱火,面帶怒容。 6耶和華問該隱:「你為什麼惱火?為什麼面帶怒容? 7如果你做得對,難道不會蒙悅納嗎?如果你做得不對,罪就蹲在你的門口要控制你,但你必須制伏罪。」

8該隱對弟弟亞伯說:「我們去田間吧!」4·8 我們去田間吧!」參照七十士譯本,希伯來文無此句。他們在田間的時候,該隱動手打亞伯,把他殺了。

9後來,耶和華問該隱:「你弟弟亞伯在哪裡?」他說:「我不知道!難道我是弟弟的看護人嗎?」 10耶和華說:「你做了什麼事?你弟弟的血從地裡向我哭訴。 11地張開口從你手上接受了你弟弟的血,你在地上必受咒詛。 12你種地,地卻不會再為你長出任何東西,你必在地上四處漂泊。」 13該隱對耶和華說:「這懲罰太重!我承受不了。 14今天你把我趕出去,使我不能再見你的面。我在地上四處漂泊,見到我的人都會殺我。」 15耶和華對他說:「不會的,因為凡殺你的,必遭受七倍的報應。」於是,耶和華在該隱身上留下一個記號,免得見到他的人殺他。 16該隱離開耶和華,來到伊甸東邊的挪得住下來。

該隱的後代

17該隱和妻子同房,他的妻子就懷孕,生了以諾該隱建了一座城,用他兒子的名字給這城取名叫以諾18以諾以拿以拿米戶雅利米戶雅利瑪土撒利瑪土撒利拉麥19拉麥娶了兩個妻子,一個叫亞大,另一個叫洗拉20亞大生了亞八亞八是遊牧民族的祖先, 21亞八的弟弟猶八是吹奏樂器之人的鼻祖。 22洗拉生了土八·該隱,他是打造各種銅鐵器具的匠人4·22 他是打造各種銅鐵器具的匠人」或譯「他是銅匠、鐵匠的祖先」。,他的妹妹叫拿瑪

23一天,拉麥對他的兩個妻子說:

亞大洗拉,你們聽我的聲音;

拉麥的妻子啊,側耳聽我的話,

有人傷我,我殺了他,

青年打我,我宰了他。

24該隱的遭受七倍的報應,

拉麥的遭受七十七倍的報應。」

塞特和以挪士

25亞當又與妻子夏娃同房,夏娃生了一個兒子,取名叫塞特,因為她說:「上帝賜我另一個兒子來代替亞伯,因為該隱殺了他。」 26塞特生了一個兒子,給他取名叫以挪士。那時候,人才開始求告耶和華。

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 4:1-26

ቃየንና አቤል

1አዳም ሚስቱን ሔዋንን ተገናኛት፤ እርሷም ፀንሳ ቃየንን4፥1 ቃየን የሚለው ስም ማምጣት ወይም ማግኘት የሚል ትርጕም ካላቸው የዕብራይስጥ ቃላት ጋር ተመሳሳይ ድምፅ አለው ወለደች፤ “በእግዚአብሔር (ያህዌ) ርዳታ ወንድ ልጅ አገኘሁ” አለች። 2ደግሞም ወንድሙን አቤልን ወለደች።

አቤል የበግ እረኛ፣ ቃየንም ዐራሽ ነበር። 3በአንድ ወቅት፣ ቃየን ከምድር ፍሬ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሥዋዕት አቀረበ። 4አቤልም መጀመሪያ ከተወለዱት በጎች መካከል ስባቸውን መሥዋዕት አድርጎ አቀረበ። እግዚአብሔር (ያህዌ) ወደ አቤልና ወደ መሥዋዕቱ ተመለከተ፤ 5በቃየንና በመሥዋዕቱ ግን አልተደሰተም፤ ስለዚህ ቃየን ክፉኛ ተናደደ፤ ፊቱም ጠቈረ።

6እግዚአብሔር አምላክም (ያህዌ ኤሎሂም) ቃየንን እንዲህ አለው፤ “ለምን ተናደድህ? ለምንስ ፊትህ ጠቈረ? 7መልካም ብታደርግ ተቀባይነትን አታገኝምን? መልካም ባታደርግ ግን፣ ኀጢአት በደጅህ እያደባች ናት፤ ልታሸንፍህ ትፈልጋለች፤ አንተ ግን ተቈጣጠራት።”

8ቃየንም ወንድሙን አቤልን፣ “እስቲ ና፤ ወደ መስኩ እንውጣ”4፥8 እስቲ ና፣ ወደ መስኩ እንውጣ የሚለው ሐረግ በኦሪተ ሳምራውያን፣ በሰብዓ ሊቃናት፣ በቩልጌትና፣ በሱርስት የሚገኝ ሲሆን በማሶሬቲክ ጽሑፍ ውስጥ ግን የለም አለው፤ በመስኩም ሳሉ፣ ቃየን ወንድሙን አቤልን አጠቃው፤ ገደለውም።

9ከዚያም፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) ቃየንን፣ “ወንድምህ አቤል የት ነው?” አለው።

ቃየንም፣ “አላውቅም፤ እኔ የወንድሜ ጠባቂ ነኝን?” ሲል መለሰ።

10እግዚአብሔርም (ያህዌ) እንዲህ አለ፤ “ምንድን ነው ያደረግኸው? የወንድምህ ደም ከምድር ወደ እኔ ይጮኻል። 11እንግዲህ የተረገምህ ነህ፤ የወንድምህን ደም ከእጅህ ለመቀበል አፏን ከከፈተችው መሬት ትሰደዳለህ። 12ብታርሳትም ፍሬዋን አትለግስህም፤ በምድር ላይ ኰብላይና ተንከራታች ትሆናለህ።” 13ቃየንም እግዚአብሔርን (ያህዌ) እንዲህ አለው፤ “ቅጣቴ ልሸከመው ከምችለው በላይ ነው። 14እነሆ፤ ዛሬ ከምድሪቱ አባረርኸኝ፤ ከፊትህም እሸሸጋለሁ፤ በምድር ላይ ኰብላይና ተንከራታች እሆናለሁ፤ የሚያገኘኝም ሁሉ ይገድለኛል።”

15እግዚአብሔር (ያህዌ) ግን፣ “የለም! እንደርሱ አይሆንም፤4፥15 ዕብራይሰጡ ከሰብዓ ሊቃናት፣ ከቩልጌትና ከሱርስቱ ጋር ተመሳሳይ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን መልካም ይለዋል። ማንም ቃየንን ቢገድል፣ ሰባት ዕጥፍ የበቀል ቅጣት ይቀበላል” አለው፤ ስለዚህ፣ ያገኘው ሁሉ እንዳይገድለው እግዚአብሔር (ያህዌ) በቃየን ላይ ምልክት አደረገለት። 16ቃየንም ከእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ወጥቶ ሄዶ፣ ከዔድን በስተ ምሥራቅ በምትገኝ ኖድ4፥16 ኖድ ማለት መቅበዝበዝ ማለት ነው (12 እና 14 ይመ)። በተባለች ምድር ተቀመጠ።

17ቃየን ሚስቱን ተገናኛት፤ እርሷም ፀንሳ ሄኖክን ወለደች። ቃየን የቈረቈረውን ከተማ በልጁ ስም ሄኖክ ብሎ ጠራው። 18ሄኖክ ኢራድን ወለደ፤ ኢራድም መሑያኤልን፣ መሑያኤልም ማቱሣኤልን፣ ማቱሣኤልም ላሜሕን ወለደ።

19ላሜሕ ሁለት ሚስቶች አገባ፤ የአንደኛዋ ስም ዓዳ፣ የሁለተኛዋም ጺላ ነበር። 20ዓዳ ያባልን ወለደች፤ እርሱም በድንኳን ለሚኖሩ ከብት አርቢዎች አባት ነበረ። 21ወንድሙም ዩባል ይባላል፤ እርሱም የበገና ደርዳሪዎችና የዋሽንት ነፊዎች አባት ነበረ። 22ሴላም ደግሞ ቱባልቃይን የተባለ ወንድ ልጅ ነበራት፤ እርሱም ከብረትና ከናስ ልዩ ልዩ መሣሪያዎችን እየቀረጸ የሚሠራ ነበር። የቱባልቃይን እኅት ናዕማ ትባል ነበር።

23ላሜሕ ሚስቶቹን እንዲህ አላቸው፤

“ዓዳና ጺላ ሆይ ስሙኝ፤

የላሜሕ ሚስቶች ሆይ አድምጡኝ፤

አንድ ሰው ቢያቈስለኝ፣

ጕልማሳው ቢጐዳኝ፣ ገደልሁት፤4፥23 ወይም እገድላለሁ

24ቃየንን የሚገድል ሰባት ጊዜ ቅጣት ካገኘው፣

የላሜሕ ገዳይማ ሰባ ሰባት ጊዜ ቅጣት ያገኘዋል።”

25አዳም እንደ ገና ሚስቱን ተገናኛት፤ እርሷም ወንድ ልጅ ወለደች። “ቃየን በገደለው በአቤል ፈንታ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ምትክ ሰጠኝ” ስትል ስሙን ሴት4፥25 ሴት ማለት ሰጠ ሳይሆን አይቀርም። ብላ ጠራችው። 26ለሴትም ደግሞ ወንድ ልጅ ተወለደለት፤ ስሙንም ሄኖስ አለው።

በዚያም ዘመን ሰዎች የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ስም መጥራት4፥26 ወይም ማወጅ ጀመሩ።