創世記 13 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

創世記 13:1-18

亞伯蘭與羅得分道揚鑣

1亞伯蘭帶著妻子、侄兒羅得和所有的一切離開埃及去南地。 2這時候亞伯蘭已經擁有很多牲畜和金銀。 3-4他從南地漸漸遷移到伯特利,到了他從前在伯特利中間搭帳篷和築壇的地方。他又在那裡求告耶和華。 5亞伯蘭同行的羅得也有牛群、羊群和帳篷。 6他們的牲畜很多,那地方容納不下,他們無法住在一起。 7亞伯蘭的牧人和羅得的牧人彼此爭執。那時,迦南人和比利洗人也住在那裡。

8亞伯蘭羅得說:「我們不該彼此爭執,我們的牧人也不該互相爭執,因為我們是骨肉至親。 9整片土地不就在你面前嗎?我們分開吧。如果你往左邊去,我就往右邊走;如果你往右邊去,我就往左邊走。」 10羅得舉目眺望,看見整個約旦河平原,遠至瑣珥,水源充足。在耶和華還沒有毀滅所多瑪蛾摩拉之前,那地方就好像耶和華的伊甸園,又像埃及11於是,羅得選了整個約旦河平原,向東遷移,他們便分開了。 12亞伯蘭住在迦南羅得則住在平原的城邑裡,並漸漸把帳篷遷移到所多瑪附近。 13所多瑪人極其邪惡,在耶和華眼中罪惡滔天。

14羅得離開後,耶和華對亞伯蘭說:「從你站的地方向東西南北眺望, 15你所能看見的地方,我都要賜給你和你的後代,直到永遠。 16我要使你的後代多如地上的塵土,人若能數算地上的塵土,才能數算你的後代。 17你起來走遍這片土地,因為我要把這片土地賜給你。」 18亞伯蘭就把帳篷遷移到希伯崙幔利的橡樹那裡居住,在那裡為耶和華築了一座祭壇。

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 13:1-18

የአብራምና የሎጥ መለያየት

1አብራም ሚስቱንና ንብረቱን ሁሉ ይዞ ከግብፅ ወደ ኔጌብ ሄደ፤ ሎጥም አብሮት ነበረ። 2አብራም በከብት፣ በብርና በወርቅ እጅግ በልጽጎ ነበር።

3አብራም ከኔጌብ ተነሥቶ እስከ ቤቴል ተጓዘ፤ ቀድሞ በቤቴልና በጋይ መካከል ድንኳኑን ከተከለበት፣ 4ለመጀመሪያ ጊዜም መሠዊያ ካቆመበት ስፍራ ደረሰ፤ በዚያም የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ስም ጠራ።

5ከአብራም ጋር አብሮት ይጓዝ የነበረው ሎጥ በጎች፣ ከብቶችና ድንኳኖች ነበሩት። 6ሆኖም ሁለቱ አንድ ላይ ሲኖሩ ስፍራው አልበቃቸውም፤ ንብረታቸው እጅግ ብዙ ስለ ነበር፣ አብረው መኖር አልቻሉም። 7ይህም በመሆኑ በአብራምና በሎጥ እረኞች መካከል ጠብ ተፈጠረ። በዚያን ዘመን ከነዓናውያንና ፌርዛውያን በዚያው አገር ይኖሩ ነበር።

8አብራምም ሎጥን እንዲህ አለው፤ “እኛ ወንድማማቾች ነንና፣ በአንተና በእኔ ወይም በእረኞቻችን መካከል ጠብ ሊኖር አይገባም። 9ይኸው እንደምታየው አገሩ ሰፊ ነው፤ ብንለያይ ይሻላል። አንተ ግራውን ብትመርጥ፣ እኔ ወደ ቀኝ እሄዳለሁ፤ አንተ ቀኙን ብትመርጥ፣ እኔ ወደ ግራ አመራለሁ።”

10ሎጥ ዐይኑን አቅንቶ ሲመለከት፣ የዮርዳኖስ ረባዳ ሜዳ እንደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ገነት፣ በዞዓር አቅጣጫ እንዳለው እንደ ግብፅ ምድር ውሃማ ቦታ ሆኖ አገኘው። እንዲህም የነበረው እግዚአብሔር (ያህዌ) የሰዶምንና የገሞራን ከተሞች ከማጥፋቱ በፊት ነው። 11ሎጥ የዮርዳኖስን ረባዳ ሜዳ በሙሉ መርጦ ወደ ምሥራቅ አመራ፤ ሁለቱ ሰዎች በዚሁ ተለያዩ። 12አብራም መኖሪያውን በከነዓን ምድር አደረገ፤ ሎጥ ግን በረባዳው ሜዳ ውስጥ ባሉት ከተሞች መካከል በሰዶም አቅራቢያ ድንኳኑን ተከለ። 13የሰዶም ሰዎች ግን ክፉዎችና በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት እጅግ ኀጥኣን ነበሩ።

14ሎጥ ከተለየው በኋላ እግዚአብሔር (ያህዌ) አብራምን እንዲህ አለው፤ “ካለህበት ስፍራ ቀና ብለህ ወደ ሰሜንና ወደ ደቡብ፣ ወደ ምሥራቅና ወደ ምዕራብ ተመልከት፤ 15ዐይንህ የሚያየውን ምድር ሁሉ ለአንተና ለዘርህ ለዘላለም እሰጣለሁ። 16ዘርህን እንደ ምድር ትቢያ አበዛዋለሁ፤ ማንም የምድርን ትቢያ ሊቈጥር እንደማይችል ሁሉ የአንተም ዘር የማይቈጠር ይሆናል። 17እንግዲህ ምድሪቱን ስለምሰጥህ ተነሣ፤ በርዝመቷም፣ በስፋቷም ተመላለስባት።”

18አብራምም ድንኳኑን ነቀለ፤ ሄዶም ኬብሮን በሚገኙት ትልልቅ የመምሬ ዛፎች አጠገብ ተቀመጠ፤ በዚያም ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሠዊያ ሠራ።