傳道書 7 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

傳道書 7:1-29

1美好的名聲勝過珍貴的膏油,

人死之日勝過出生之時。

2探望喪家勝過參加宴席,

因為死亡是每個人的結局,

活著的人要把這事銘記在心。

3哀傷勝過歡笑,

因為哀傷磨煉人的心靈。

4智者的心思考生死大事,

愚人的心只顧作樂。

5聽智者的責備,

勝過聽愚人的頌歌。

6愚人的笑聲像鍋底下燒荊棘的噼啪聲。

這也是虛空。

7欺壓使智者變愚昧,

賄賂敗壞人心。

8事情的結局勝過事情的開端;

恆久忍耐勝過心驕氣傲。

9不要輕易發怒,

因為愚人心懷怒氣。

10不要問為什麼過去比現在好,

因為這樣問不明智。

11智慧如同產業一樣美好,

有益於得見日光的世人。

12智慧如同金錢,

是一種保障,

能保全智者的生命。

這就是知識的好處。

13你應當思想上帝的作為,

因為上帝弄彎的,

誰能使它變直呢?

14順境時要快樂,

逆境時要思想:

兩者都是上帝的安排,

好叫人不能預知將來。

15在我虛空的一生中,我見過義人行義,反而滅亡;惡人行惡,卻享長壽。 16為人不要過分正直,也不要過於聰明,何必自取毀滅呢? 17不要過分邪惡,也不要做愚人,何必時候未到就死呢? 18最好是持守這個教訓也不放鬆那個教訓,因為敬畏上帝的人必避免兩個極端。 19智慧使一個智者比城裡十個官長更有能力。 20誠然,在地上無法找到一個一生行善、從未犯罪的義人。 21你不要斤斤計較別人所說的每一句話,免得聽見你的僕人咒詛你, 22因為你心裡知道自己也曾多次咒詛別人。 23我用智慧試驗過這一切。我說:「我要做智者」,誰知智慧卻離我甚遠。 24智慧如此遙不可及、深不可測,誰能找得到呢? 25我用心去認識、探究、追尋智慧和事物的原委,並去認識邪惡帶來的愚昧和無知帶來的狂妄。 26我發現有的婦人比死亡更苦毒,她是個陷阱,心如網羅,手像鎖鏈。敬畏上帝的人避開她,罪人卻被她俘虜。 27-28傳道者說:「看啊,我事事反復探索,要查明萬事之理,卻沒有尋獲。但我發現在一千個男子中還可以找到一位正直人,在眾女子中卻未找到一位。 29我只發現一件事,上帝造的人本來正直,人卻找出各種詭計。」

New Amharic Standard Version

መክብብ 7:1-29

ጥበብ

1መልካም ስም ከመልካም ሽቱ ይበልጣል፤

ከልደትም ቀን የሞት ቀን ይሻላል።

2ወደ ግብዣ ቤት ከመሄድ፣

ወደ ሐዘን ቤት መሄድ ይሻላል፤

ሞት የሰው ሁሉ ፍጻሜ ነውና፤

ሕያው የሆነም ይህን ልብ ማለት ይገባዋል።

3ሐዘን ከሣቅ ይሻላል፤

ያዘነ ፊት ለልብ መልካም ነውና።

4የጠቢባን ልብ በሐዘን ቤት ነው፤

የሞኞች ልብ ግን በደስታ ቤት ነው።

5የሞኞችን መዝሙር ከመስማት፣

የጠቢባንን ሰዎች ተግሣጽ መስማት ይሻላል።

6የሰነፎች ሣቅ፣

ከድስት ሥር እንደሚንጣጣ የእሾኽ ማገዶ ነው፤

ይህም ደግሞ ከንቱ ነው።

7ግፍ ጠቢብን ሞኝ ያደርጋል፤

ጕቦም ልብን ያበላሻል።

8የአንድ ነገር ፍጻሜ ከጅማሬው ይሻላል፤

ትዕግሥተኛም ከትዕቢተኛ ይሻላል።

9የሞኞች ቍጣ በዕቅፋቸው ውስጥ ስለሆነ፣

በመንፈስህ ለቍጣ አትቸኵል።

10አንተም፣ “ከእነዚህ ቀናት የቀድሞዎቹ ለምን ተሻሉ?” አትበል፤

እንዲህ ያሉትን ጥያቄዎች መጠየቅ ጠቢብነት አይደለምና።

11ጥበብ እንደ ርስት መልካም ነገር ነው፤

ጠቃሚነቱም ፀሓይን ለሚያዩ ሰዎች ነው።

12ገንዘብ ጥላ ከለላ እንደ ሆነ ሁሉ፣

ጥበብም ጥላ ከለላ ነው፤

የዕውቀት ብልጫዋ ግን፣

ጥበብ የባለቤቷን ሕይወት መጠበቋ ነው።

13እግዚአብሔር ያደረገውን ተመልከት፤

እርሱ ያጣመመውን፣

ማን ሊያቃናው ይችላል?

14ጊዜው መልካም ሲሆን፣ ደስ ይበልህ፤

ጊዜው ክፉ ሲሆን ግን ይህን ዐስብ፤

እግዚአብሔር አንዱን እንዳደረገ፣

ሌላውንም አድርጓል፤

ስለዚህ ሰው ስለ ወደ ፊት ሁኔታው፣

ምንም ሊያውቅ አይችልም።

15በዚህ ከንቱ በሆነው ሕይወቴ እነዚህን ሁለቱን ነገሮች አይቻለሁ፤

ጻድቅ በጽድቁ ሲጠፋ፣

ኀጥእም በክፋቱ ዕድሜው ሲረዝም።

16እጅግ ጻድቅ፣

እጅግም ጠቢብ አትሁን፤

ራስህን ለምን ታጠፋለህ?

17እጅግ ክፉ አትሁን፤

ሞኝም አትሁን፤

ለምንስ ያለ ቀንህ ትሞታለህ?

18አንዱን ይዞ ሌላውንም አለመልቀቅ መልካም ነው፤

እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው

ጽንፈኝነትን ያስወግዳል7፥18 ወይም ሁለቱንም ይከተላቸዋል

19በአንድ ከተማ ካሉ ዐሥር ገዦች ይልቅ፣

ጥበብ ጠቢቡን ሰው ኀያል ታደርገዋለች።

20ትክክለኛውን ነገር የሚያደርግና ፈጽሞ ኀጢአት የማይሠራ

ጻድቅ ሰው በምድር ላይ የለም።

21የሚነገረውን ቃል ሁሉ ለማዳመጥ አትሞክር፤

አለዚያ አገልጋይህ ሲረግምህ ትሰማ ይሆናል፤

22ብዙ ጊዜ አንተ ራስህ፣

ሌሎችን እንደ ረገምህ ልብህ ያውቃልና።

23እኔም ይህን ሁሉ በጥበብ ፈትኜ፣

“ጠቢብ ለመሆን ቈርጫለሁ” አልሁ፤

ይህ ግን ከእኔ የራቀ ነበር።

24ጥበብ ምንም ይሁን ምን፣

እጅግ ጥልቅና ሩቅ ነው፤

ማንስ ሊደርስበት ይችላል?

25ስለዚህ ጥበብንና የነገሮችን አሠራር ለመመርመርና ለማጥናት፣

የክፋትን መጥፎነት፣

የሞኝነትንም እብደት ለማስተዋል፣

አእምሮዬን መለስሁ።

26ልቧ ወጥመድ፣

እጆቿም እግር ብረት የሆኑ፣

አሽክላ የሆነች፣

ከሞት የከፋችዋን ሴት አገኘሁ፤

እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ከእጇ ያመልጣል፤

ኀጢአተኛውን ግን አጥምዳ ትይዘዋለች።

27ሰባኪው7፥27 ወይም የጉባኤ መሪ እንዲህ ይላል፤ “እነሆ፤ መርምሬ ያገኘሁት ነገር ይህ ነው፤

“የነገሮችን ብልኀት መርምሮ ለማግኘት፣

አንዱን በአንዱ ላይ በመጨመር፣

28ገና በመመርመር ላይ ሳለሁ፣

ግን ያላገኘሁት፣

ከሺሕ ወንዶች መካከል አንድ ቅን ሰው አገኘሁ፣

በእነዚያ ሁሉ መካከል ግን አንዲት ቅን ሴት አላገኘሁም።

29ይህን አንድ ነገር ብቻ አገኘሁ፤

እግዚአብሔር ሰውን ቅን አድርጎ መሥራቱን፣

ሰዎች ግን ውስብስብ ዘዴ ቀየሱ።”