傳道書 5 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

傳道書 5:1-20

敬畏上帝

1你進入上帝的殿時要小心謹慎,近前傾聽勝過愚人獻祭,因為他們不知道自己是在作惡。 2在上帝面前不要冒失開口,不可急於發言,因為祂在天上,你在地上。所以,你要少言寡語。 3事務繁雜,夜裡多夢;多言多語,顯出愚昧。 4你向上帝許願,不可遲遲不還,因為祂不喜歡這樣的愚人。要還所許的願。 5與其許了願不還,倒不如不許。 6不要在言語上犯罪,也不要在祭司5·6 祭司」希伯來文是「使者」。面前說許錯了願。為什麼用言語惹上帝發怒,以致祂摧毀你手中的工作呢? 7多夢多言都是虛空。你只要敬畏上帝!

財富虛空

8若你在某地看見窮人受欺壓,公平正義被扭曲,不要震驚,因為官上有官,在眾官之上還有更高的官。 9況且,地的出產滋養萬物,就是君王也需要從田地得到供應。 10貪愛錢財的,金銀不能使他滿足;貪圖富裕的,再多的利益也不能叫他稱心。這也是虛空! 11財富增加,消費的人也增加,這對財富的主人有什麼益處呢?只是過眼雲煙罷了! 12勞力的人不管吃多吃少,總是睡得香甜;富人的萬貫家財卻害得他不能成眠。 13我看到日光之下有一件可悲的事:有人積攢財寶,反而害了自己。 14經營不善,便財富盡失,什麼也不能留給兒子。 15人怎樣從母腹空空而來,也必照樣空空而去;勞碌一生,什麼也不能帶走。 16這是多麼可悲啊!人怎樣來,也要怎樣去,為風勞碌有什麼益處呢? 17他一生活在黑暗中,飽受煩惱、病痛和憤怒的困擾。 18我認為人生最美最善的是,在上帝所賜的短暫歲月中盡情吃喝,享受自己在日光之下勞苦得來的成果。因為這是人當得的。 19上帝不單給人財富,也叫他能吃能喝,享用自己所當得的,並在勞碌中得到快樂,這都是上帝的恩賜。 20他不用擔憂自己壽命的長短,因為上帝使他心裡充滿喜樂。

New Amharic Standard Version

መክብብ 5:1-20

እግዚአብሔርን ፍራ

1ወደ እግዚአብሔር ቤት ስትሄድ እግርህን ጠብቅ። ለመስማት መቅረብ የሰነፎችን መሥዋዕት ከማቅረብ ይበልጣል፤ እነርሱ ክፉ እንደሚሠሩ አያውቁምና።

2በአፍህ አትፍጠን፤

በእግዚአብሔርም ፊት ማንኛውንም ነገር ለመናገር፣

በልብህ አትቸኵል፤

እግዚአብሔር በሰማይ፣

አንተ ደግሞ በምድር ነህ፤

ስለዚህ ቃልህ ጥቂት ይሁን።

3በሥራ ብዛት ሕልም እንደሚታይ፣

ብዙ ቃል ባለበትም የሞኝ ንግግር ይገለጣል።

4ለእግዚአብሔር ስእለትን በተሳልህ ጊዜ ለመፈጸም አትዘግይ፤ በሰነፎች ደስ አይለውምና፤ ስእለትህን ፈጽም። 5ስእለት ተስሎ ካለመፈጸም፣ አለመሳል ይሻላል። 6አንደበትህ ወደ ኀጢአት እንዲመራህ አትፍቀድ፤ ለቤተ መቅደስ መልእክተኛም፣ “የተሳልሁት በስሕተት ነበር” አትበል። እግዚአብሔር በተናገርኸው ተቈጥቶ የእጅህን ሥራ ለምን ያጥፋ? 7ብዙ ሕልምና ብዙ ቃል ከንቱ ነው፤ ስለዚህ እግዚአብሔርን ፍራ።

ባለጠግነት ከንቱ ነው

8በአገር ውስጥ ድኻ ተጨቍኖ፣ ፍትሕ ተጓድሎ፣ መብትም ተረግጦ ብታይ፣ እንደነዚህ ባሉ ነገሮች አትደነቅ፤ ምክንያቱም አንዱን አለቃ የበላዩ ይመለከተዋል፤ በእነዚህ በሁለቱም ላይ ሌሎች ከፍ ያሉ አሉ። 9ከምድሩ የሚገኘው ትርፍ ለሁሉም ነው፤ ንጉሡም ራሱ የሚጠቀመው ከዕርሻ ነው።

10ገንዘብን የሚወድድ፣ ገንዘብ አይበቃውም፤

ብልጽግናም የሚወድድ፣ በትርፉ አይረካም፤

ይህም ከንቱ ነው።

11ሀብት በበዛ ቍጥር፣

ተጠቃሚውም ይበዛል፤

በዐይኑ ብቻ ከማየት በቀር

ታዲያ፣ ለባለቤቱ ምን ይጠቅመዋል?

12ጥቂትም ይሁን ብዙ ቢበላ፣

የሠራተኛ እንቅልፍ ጣፋጭ ነው፤

የሀብታም ሰው ብልጽግና ግን

እንቅልፍ ይነሣዋል።

13ከፀሓይ በታች የሚያሳዝን ክፉ ነገር አየሁ፦

ይህም ለባለቤቱ ጕዳት የተከማቸ ሀብት፣

14ወይም በአንድ መጥፎ አጋጣሚ የጠፋ ብልጽግና ነው፤

ልጅ ሲወልድም፣

ለእርሱ የሚያስቀርለት ምንም ነገር አይኖርም።

15ሰው ከእናቱ ማሕፀን ዕራቍቱን ይወለዳል፤

እንደ መጣው እንዲሁ ይመለሳል።

ከለፋበትም ነገር፣

አንድም እንኳ በእጁ ይዞ ሊሄድ አይችልም።

16ይህ ደግሞ እጅግ ክፉ ነገር ነው፤

ሰው እንደ መጣ እንዲሁ ይሄዳል፤

የሚደክመው ለነፋስ ስለሆነ፣

ትርፉ ምንድን ነው?

17በብዙ ጭንቀት፣ መከራና ብስጭት፣

ዘመኑን ሁሉ በጨለማ ውስጥ ይበላል።

18የሰው ዕጣው ይህ ስለሆነ፣ እግዚአብሔር በሰጠው በጥቂት ዘመኑ ከፀሓይ በታች በሚደክምበት ነገር ርካታን ያገኝ ዘንድ፣ መብላቱና መጠጣቱም መልካምና ተገቢ መሆኑን ተገነዘብሁ። 19እግዚአብሔር ለሰው ባለጠግነትና ሀብት መስጠቱ፣ እንዲደሰትበትም ማስቻሉ፣ ዕጣውን እንዲቀበልና በሥራውም እንዲደሰት ማድረጉ፣ ይህ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው። 20እግዚአብሔር የልብ ደስታ ስለሚሰጠውም በሕይወቱ ዘመን ያሉትን ቀናት እምብዛም አያስባቸውም።