傳道書 3 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

傳道書 3:1-22

萬物有時

1天下萬物都有定期,

凡事都有定時。

2出生有時,死亡有時;

耕種有時,拔出有時;

3殺戮有時,醫治有時;

拆毀有時,建造有時;

4哭泣有時,歡笑有時;

哀傷有時,雀躍有時;

5拋石有時,堆石有時3·5 拋石有時,堆石有時」意義不明,有猶太拉比說是「同房有時,分房有時」。

擁抱有時,避開有時;

6尋找有時,遺失有時;

保存有時,丟棄有時;

7撕裂有時,縫合有時;

沉默有時,發言有時;

8愛慕有時,憎惡有時;

爭戰有時,和好有時。

9那麼,人勞碌做工有什麼益處呢? 10我察覺上帝給世人重擔,使他們忙碌不休。 11祂使萬事各按其時變得美好,又把永恆的意識放在人心裡,人卻不能測透上帝從始至終的作為。 12我認識到,人生在世沒有什麼比歡樂、享受更好。 13人人都該吃喝、享受自己勞苦的成果,這是上帝的恩賜。 14我知道,上帝所做的都會存到永遠,誰也不能增減。祂這樣安排是叫人敬畏祂。 15現在的事並不是新事,未來的事也早已發生過。上帝使過去的事再次出現。

世間的不公

16我又看到日光之下,即使在公道和正義之地也有邪惡。 17我心裡想:「不論義人或惡人,上帝必審判,因為萬事萬務都有受審之時。」 18我又想:「至於世人,上帝試驗他們,是要他們知道自己與獸類無異。 19因為人和獸的際遇並無分別,兩者都難逃一死,活著都靠一口氣。人並不比獸強,一切都是虛空。 20兩者都同歸一處,出於塵土,也歸於塵土。 21誰知道人的氣息3·21 氣息」或譯「靈」,本節同。會向上升,獸的氣息會降到地下呢?」 22因此,我覺得沒有什麼比人享受工作之樂更好,因為這是人當得的。人死後,誰能使他看到世間的事呢?

New Amharic Standard Version

መክብብ 3:1-22

ለሁሉም ጊዜ አለው

1ለሁሉም ነገር ጊዜ አለው፤

ከሰማይ በታች ለሚከናወነው ለማንኛውም ነገር ወቅት አለው፤

2ለመወለድ ጊዜ አለው፤ ለመሞትም ጊዜ አለው፤

ለመትከል ጊዜ አለው፤ ለመንቀልም ጊዜ አለው፤

3ለመግደል ጊዜ አለው፤ ለማዳንም ጊዜ አለው፤

ለማፍረስ ጊዜ አለው፤ ለመገንባትም ጊዜ አለው፤

4ለማልቀስ ጊዜ አለው፤ ለመሣቅም ጊዜ አለው፤

ለሐዘን ጊዜ አለው፤ ለጭፈራም ጊዜ አለው፤

5ድንጋይ ለመጣል ጊዜ አለው፤ ድንጋይ ለመሰብሰብም ጊዜ አለው፤

ለመተቃቀፍ ጊዜ አለው፤ ለመለያየትም ጊዜ አለው፤

6ለመፈለግ ጊዜ አለው፤ ለመተው ጊዜ አለው፤

ለማስቀመጥ ጊዜ አለው፤ አውጥቶ ለመጣልም ጊዜ አለው፤

7ለመቅደድ ጊዜ አለው፤ ለመስፋትም ጊዜ አለው፤

ለዝምታ ጊዜ አለው፤ ለመናገርም ጊዜ አለው፤

8ለመውደድ ጊዜ አለው፤ ለመጥላትም ጊዜ አለው፤

ለጦርነት ጊዜ አለው፤ ለሰላምም ጊዜ አለው።

9ሠራተኛ ከጥረቱ የሚያገኘው ትርፍ ምንድን ነው? 10ሰዎች ይደክሙበት ዘንድ እግዚአብሔር የሰጣቸውን ከባድ የሥራ ጫና አየሁ። 11ሁሉንም ነገር በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው፤ በሰዎችም ልብ ዘላለማዊነትን አኖረ፤ ይሁን እንጂ እግዚአብሔር ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ያደረገውን ማወቅ አይችሉም። 12ለሰዎች፣ በሕይወት እያሉ ደስ ከመሰኘትና መልካምን ነገር ከማድረግ የተሻለ ነገር እንደሌለ ዐወቅሁ። 13ሰው ሁሉ ይበላና ይጠጣ ዘንድ፣ በሚደክምበትም ሁሉ ርካታን ያገኝ ዘንድ ይህ የእግዚአብሔር ችሮታ ነው። 14እግዚአብሔር ያደረገው ሁሉ ለዘላለም እንደሚኖር ዐውቃለሁ፤ በእርሱ ላይ ምንም አይጨመርም፤ ከእርሱም ምንም አይቀነስም፤ ሰዎች ያከብሩት ዘንድ ይህን አደረገ።

15አሁን ያለው ከዚህ በፊት የነበረው ነው፤

ወደ ፊት የሚሆነውም ቀድሞ የነበረ ነው፤

እግዚአብሔርም ያለፈውን መልሶ ይሻዋል3፥15 ወይም እግዚአብሔር ያለፈውን መልሶ ይጠራዋል

16ከፀሓይ በታችም ሌላ ነገር አየሁ፤

በፍርድ ቦታ ዐመፅ ነበር፤

በፍትሕ ቦታ ግፍ ነበር።

17እኔም በልቤ፣

“ለማንኛውም ድርጊት፣

ለማንኛውም ተግባር ጊዜ ስላለው፣

እግዚአብሔር ጻድቁንና ኀጢአተኛውን ወደ ፍርድ ያመጣቸዋል”

ብዬ አሰብሁ።

18እንዲህም ብዬ አሰብሁ፤ “ሰዎች፣ እንደ እንስሳት መሆናቸውን ያዩ ዘንድ እግዚአብሔር ይፈትናቸዋል። 19የሰው ዕድል ፈንታ እንደ እንስሳት ነው፤ ሁለቱም ዕጣ ፈንታቸው አንድ ነው፤ አንዱ እንደሚሞት፣ ሌላውም እንዲሁ ይሞታል። ሁሉ አንድ ዐይነት እስትንፋስ3፥19 ወይም መንፈስ አላቸው፤ ሰውም ከእንስሳ ብልጫ የለውም፤ ሁሉም ከንቱ ነው። 20ሁሉም ወደ አንድ ቦታ ይሄዳሉ፤ ሁሉም ከዐፈር እንደ ሆኑ፣ ተመልሰው ወደ ዐፈር ይሄዳሉ። 21የሰው መንፈስ ወደ ላይ መውጣቱን፣ የእንስሳ እስትንፋስ3፥21 ወይም የሰው መንፈስ ወደ ላይ እንደሚሄድ ወይም የእንስሳት መንፈስ ደግሞ ወደ ታች ወደ ምድር መውረዱን ማን ያውቃል?”

22ስለዚህ ለሰው ዕጣ ፈንታው ስለሆነ፣ በሥራው ከመደሰት የተሻለ ነገር እንደሌለው አየሁ፤ ከእርሱ በኋላ የሚሆነውንስ ተመልሶ እንዲያይ የሚያደርገው ማን ነው?