俄巴底亞書 1 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

俄巴底亞書 1:1-21

1俄巴底亞看到的異象。

耶和華懲罰以東

論到以東

主耶和華這樣說:

「我們從耶和華那裡聽到消息,

有位使者被派到各國,說,

『來!我們去攻打以東吧!』」

2耶和華對以東說:

「我要讓你成為列國中最弱小的國家,

使你飽受藐視。

3你住在懸崖峭壁間,

住在高山上,

自以為誰也不能把你拉下來,

但你的驕傲欺騙了你。

4即使你如鷹高飛,

在星辰間築巢,

我也必把你拉下來。

這是耶和華說的。

5「盜賊深夜洗劫你的家,

不會洗劫一空;

人們摘葡萄,不會摘光;

但你會被徹底毀滅!

6以掃1·6 以掃」又名「以東」。要被洗劫一空,

他藏的珍寶要被搜去。

7你的盟友將你逐出家園;

你的朋友欺騙你,戰勝你;

你的知己設陷阱害你,

你卻懵然不知。」

8耶和華說:「到那天,

我要毀滅以東的智者,

除掉以掃山上的明哲。

9提幔的勇士必驚慌失措,

以掃山上的人盡遭殺戮。

懲罰以東的原因

10「因你曾殘暴地對待同胞兄弟雅各

你必蒙羞,永遭毀滅。

11外族人掠奪雅各的財物,

攻入耶路撒冷抽籤分贓時,

你竟然袖手旁觀,

就像他們的同夥一樣。

12你的親族遭難之日,

你不該幸災樂禍;

猶大人被滅的日子,

你不該興高采烈;

他們遭難的日子,

你不該口出狂言;

13我子民遭難的日子,

你不該闖進他們的城;

他們遭難的日子,

你不該幸災樂禍;

他們遭難的日子,

你不該趁火打劫;

14你不該站在路口截殺那些逃亡者;

他們遭難的日子,

你不該把倖存者交給仇敵。

15「耶和華懲罰萬國的日子近了。

必按你的所作所為報應你,

你的惡行必落到自己頭上。

16你們猶大人在我的聖山上怎樣飽飲憤怒,

萬國也要照樣飲,

且要大口吞下,

直到他們完全消逝。

以色列的復興

17「然而,錫安山必成為避難所,

成為聖地。

雅各家必得到自己的產業。

18雅各家將成為火,

約瑟家將成為烈焰,

以掃家將成為碎稭,

被火焚燒、吞噬,無一人逃脫。

這是耶和華說的。

19「南地的人將佔領以掃山;

丘陵的人將佔領非利士

奪取以法蓮撒瑪利亞

便雅憫人將佔領基列

20被擄的以色列人將返回家園,

佔領遠至撒勒法一帶的土地;

耶路撒冷被擄到西法拉的人將佔領南地各城。

21拯救者必登上錫安山,

統治以掃山,

耶和華必做王掌權。」

New Amharic Standard Version

አብድዩ 1:1-21

የአብድዩ ራእይ

1ጌታ እግዚአብሔር ስለ ኤዶም እንዲህ ይላል፤

ከእግዚአብሔር ዘንድ መልእክት ሰምተናል፤

መልእክተኛውም ወደ አሕዛብ ተልኮ እንዲህ

ብሏል፤

“ተነሡ፤ እርሷን ለመውጋት እንውጣ።”

2“እነሆ፤ በአሕዛብ መካከል ታናሽ አደርግሃለሁ፤

እጅግ የተናቅህ ትሆናለህ።

3አንተ በሰንጣቃ1፥3 ወይም በሴላ ዐለት ውስጥ

የምትኖር፣

መኖሪያህንም በከፍታ ስፍራ ያደረግህ፣

ለራስህም፣

‘ማን ወደ ምድር ሊያወርደኝ ይችላል?’ የምትል፣

የልብህ ትዕቢት አታልሎሃል።

4እንደ ንስር መጥቀህ ወደ ላይ ብትወጣ፣

ጐጆህንም በከዋክብት መካከል ብታደርግ፣

ከዚያ አወርድሃለሁ”

ይላል እግዚአብሔር

5“ሌቦች ወደ አንተ ቢመጡ፣

ዘራፊዎችም በሌሊት ቢገቡ፣

የሚሰርቁት የሚፈልጉትን ያህል ብቻ አይደለምን?

ወይን ለቃሚዎች ወደ አንተ ቢመጡ፣

ጥቂት ቃርሚያ አይተዉምን?

አንተ ግን ምንኛ ጥፋት ይጠብቅሃል!

6ዔሳው ግን እንዴት ተዘረፈ?

የሸሸገውስ ሀብት ምንኛ ተመዘበረ!

7ወዳጆችህ ሁሉ ወደ ድንበር ይገፉሃል፤

ጓደኞችህ ያታልሉሃል፤ ያሸንፉህማል፤

እንጀራህን የበሉ ወጥመድ ይዘረጉብሃል፤1፥7 የዚህ ሐረግ የዕብራይስጡ ትርጓሜ በርግጠኝነት አይታወቅም።

አንተ ግን አታውቀውም።

8“በዚያ ቀን ጥበበኛ ሰዎችን ከኤዶም፣

አስተዋዮችንም ከዔሳው ተራሮች አልደመስስምን?”

ይላል እግዚአብሔር

9“ቴማን ሆይ፤ ተዋጊዎችህ ይደነግጣሉ፤

በዔሳውም ተራሮች ያለ ሁሉ፣

ተገድሎ ይጠፋል።

10በወንድምህ በያዕቆብ ላይ ስላደረግኸው ግፍ፣

በዕፍረት ትሸፈናለህ፤

ለዘላለምም ትጠፋለህ።

11እንግዶች ሀብቱን ዘርፈው ሲሄዱ፣

ባዕዳንም በበሮቹ ሲገቡ፣

በኢየሩሳሌምም ላይ ዕጣ ሲጣጣሉ፣

በዚያ ቀን ገለልተኛ ሆነህ ተመለከትህ፣

አንተም ከእነርሱ እንደ አንዱ ሆንህ።

12ክፉ ቀን በገጠመው ጊዜ፤

በወንድምህ ሥቃይ መደሰት አልነበረብህም፤

በጥፋታቸው ቀን፣ የይሁዳ ሕዝብ ሲያዝኑ

ሐሤት ማድረግ አልነበረብህም፤

በጭንቀታቸውም ቀን፣

በትዕቢት ልትናገር አይገባህም ነበር።

13በጥፋታቸው ቀን፣

በሕዝቤ በር መግባት የለብህም ነበር፤

በጥፋታቸው ቀን፣

በጭንቀታቸው መደሰት አልነበረብህም፤

በጥፋታቸው ቀን፣

ሀብታቸውን መዝረፍ አይገባህም ነበር።

14ስደተኞቻቸውን ለመግደል፣

በመንታ መንገድ መጠባበቅ አይገባህም ነበር፣

በጭንቀታቸው ቀን፣

የተረፉትን አሳልፈህ መስጠት አልነበረብህም።

15“በአሕዛብ ሁሉ ላይ፣

የእግዚአብሔር ቀን ደርሷል፤

አንተ እንዳደረግኸው፣ በአንተም ላይ ይደረጋል፤

ክፉ ሥራህም በራስህ ላይ ይመለሳል።

16እናንተ በቅዱሱ ተራራዬ እንደ ጠጣችሁ፣

አሕዛብ ሁሉ ዘወትር ይጠጣሉ፤

ይጠጣሉ፤ አብዝተውም ይጠጣሉ፤

ከዚህም በፊት እንዳልሆኑት ይሆናሉ።

17ነገር ግን በጽዮን ተራራ ነጻ መውጣት ይሆናል፤

የያዕቆብ ቤትም እርሷ የተቀደሰች ትሆናለች፤

ርስታቸውን ይወርሳሉ።

18የያዕቆብ ቤት እሳት፣

የዮሴፍም ቤት ነበልባል ይሆናል፤

የዔሳው ቤት ገለባ ይሆናል፤

ያቃጥሉታል፤ ይበሉትማል፤

ከዔሳው ቤት የሚተርፍ አይኖርም።”

እግዚአብሔር ተናግሯል።

19የኔጌብ ሰዎች፣

የዔሳውን ተራራ ይይዛሉ፤

ከተራራው ግርጌ ያሉ ሰዎችም፣

የፍልስጥኤማውያንን ምድር ይወርሳሉ፤

የኤፍሬምንና የሰማርያንም ዕርሻ ይይዛሉ፤

ብንያምም ገለዓድን ይወርሳል።

20በከነዓን ያለው ይህ የእስራኤል ስደተኞች ወገን፣

እስከ ሰራጵታ ያለውን ምድር ይወርሳል፤

በሰፋራድም ያሉ የኢየሩሳሌም ስደተኞች፣

የኔጌብን ከተሞች ይወርሳሉ።

21የዔሳውን ተራሮች ለመግዛት፣

ነጻ አውጪዎች ወደ ጽዮን ተራራ ይወጣሉ፤

መንግሥቱም የእግዚአብሔር ይሆናል።