马太福音 28 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

马太福音 28:1-20

耶稣复活

1安息日刚过,周日黎明时分,抹大拉玛丽亚和另一位玛丽亚一同到坟墓去察看。

2突然,大地剧烈地震动,上帝的天使从天而降,推开堵着墓穴的石头,坐在上面。 3他的容貌如闪电,衣裳洁白如雪。 4看守墓穴的卫兵吓得要死,浑身发抖。

5天使对那两个女人说:“不要怕,我知道你们是在找那位被钉十字架的耶稣。 6祂不在这里,正如祂所说的,祂已经复活了。你们来看,这是安放祂的地方。 7现在你们快回去,把这消息告诉祂的门徒,祂已经从死里复活,先你们一步去了加利利,你们将在那里见到祂。记住,我已经告诉你们了。”

8她们听了又惊又喜,连忙离开坟墓,跑去告诉门徒。 9忽然,耶稣迎面而来,对她们说:“愿你们平安!”她们就上前抱住祂的脚敬拜祂。

10耶稣对她们说:“不要害怕。去告诉我的弟兄,叫他们到加利利去,他们将在那里见到我。”

行贿造谣

11她们还在赶路的时候,有些守墓的卫兵已经进城把整件事告诉祭司长。 12祭司长和长老聚集商议,决定用重金买通守墓的卫兵,又吩咐他们: 13“你们就说,‘半夜里我们熟睡的时候,耶稣的门徒把祂的尸体偷走了。’ 14如果这件事传到总督那里,我们一定会替你们出面,保你们无事。” 15守卫收下钱,便依照吩咐去做。于是,这说法在犹太人中一直流传到今天。

大使命

16十一个门徒赶到加利利,到了耶稣和他们约定的山上, 17看到耶稣就敬拜祂,但有些人仍然心存疑惑。 18耶稣上前对门徒说:

“天上地下所有的权柄都交给我了。 19所以,你们要去使万民做我的门徒,奉父、子、圣灵的名给他们施洗, 20教导他们遵守我吩咐你们的一切。记住,我必常与你们同在,一直到世界的末了。”

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 28:1-20

የኢየሱስ ከሙታን መነሣት

28፥1-8 ተጓ ምብ – ማር 16፥1-8ሉቃ 24፥1-10

1ሰንበት ካለፈ በኋላ፣ በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን ጎሕ ሲቀድድ፣ ማርያም መግደላዊትና ሌላዋ ማርያም መቃብሩን ሊያዩ ሄዱ።

2በድንገት ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፤ የጌታም መልአክ ከሰማይ ወርዶ ወደ መቃብሩ በመሄድ ድንጋዩን አንከባልሎ በላዩ ላይ ተቀመጠበት፤ 3መልኩ እንደ መብረቅ ብሩህ፣ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ነበር። 4ጠባቂዎቹ መልአኩን ከመፍራት የተነሣ ተንቀጠቀጡ፤ እንደ በድንም ሆኑ።

5መልአኩም ሴቶቹን እንዲህ አላቸው፤ “አትፍሩ፤ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንደምትፈልጉ ዐውቃለሁና፤ 6እርሱ በዚህ የለም፤ እንደ ተናገረው ተነሥቷል፤ ኑና ተኝቶበት የነበረውን ቦታ እዩ። 7አሁንም ፈጥናችሁ ሂዱና ለደቀ መዛሙርቱ፣ ‘ከሙታን ተነሥቷል፤ ቀድሟችሁ ወደ ገሊላ ይሄዳል፤ በዚያ ታዩታላችሁ’ ብላችሁ ንገሯቸው። እንግዲህ ነግሬአችኋለሁ!”

8ሴቶቹም በፍርሀትና በደስታ ተሞልተው ለደቀ መዛሙርቱ ለመንገር በፍጥነት እየሮጡ የመቃብሩን ስፍራ ትተው ሄዱ። 9ወዲያው ኢየሱስ አገኛቸውና፣ “ሰላም ለእናንተ ይሁን!” አላቸው። እነርሱም ወደ ኢየሱስ ቀርበው እግሩን ይዘው ሰገዱለት። 10ኢየሱስም፣ “አትፍሩ፤ ሂዱና ወደ ገሊላ እንዲሄዱ ለወንድሞቼ ንገሯቸው፤ በዚያ ያዩኛል” አላቸው።

የጠባቂዎች ምስክርነት

11ሴቶቹ በመንገድ ላይ ሳሉ፣ ከጠባቂዎቹ ጥቂቶቹ ወደ ከተማ በመሄድ የሆነውን ሁሉ ለካህናት አለቆች አወሩላቸው። 12የካህናት አለቆችም ከሽማግሌዎች ጋር ተሰብስበው ተማከሩ፤ ለወታደሮቹ በቂ ገንዘብ በመስጠት 13እንዲህ አሏቸው፤ “ ‘ተኝተን ሳለን ደቀ መዛሙርቱ በሌሊት መጥተው ሰረቁት’ በሉ፤ 14ይህ ወሬ በገዥው ዘንድ ቢሰማ እንኳ፣ እኛ እናስረዳዋለን፤ ምንም ክፉ ነገር እንዳይደርስባችሁ እናደርጋለን።” 15ወታደሮቹም ገንዘቡን ተቀብለው እንደ ታዘዙት አደረጉ። ይህም ታሪክ እስከ ዛሬ ድረስ በአይሁዶች ዘንድ በሰፊው እንደ ተሠራጨ ነው።

ታላቁ ተልእኮ

16ከዚያም ዐሥራ አንዱ ደቀ መዛሙርት በገሊላ ወዳለው ኢየሱስ ወዳመለከታቸው ተራራ ሄዱ። 17ባዩትም ጊዜ ሰገዱለት፤ ጥቂቶች ግን ተጠራጠሩ። 18ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱ ወዳሉበት ቀርቦ እንዲህ አላቸው፤ “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጥቶኛል፤ 19ስለዚህ ሂዱና ሕዝቦችን ሁሉ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ 20ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ አስተምሯቸው፤ እኔም እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።”