雅歌 3 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

雅歌 3:1-11

1我夜晚躺在床上,

思念着我心爱的人;

我寻找他,却找不到。

2我要起来寻遍城里的大街小巷,

我要寻找我心爱的人。

我寻找他,却寻不到。

3遇上了城中巡逻的守卫,

我就问他们:“你们看到我心爱的人了吗?”

4我刚离开他们,便找到了我心爱的人。

我拉着他,不让他走;

我把他带回娘家,

到怀我者的卧室。

5耶路撒冷的少女啊!

我指着羚羊和田野的母鹿吩咐你们,

不要叫醒或惊动爱情,

等它自发吧。

耶路撒冷的少女:

6那从旷野上来,形状像烟柱,

散发着商人贩卖的没药、乳香等各样芬芳之气的是什么呢?

7看啊,是所罗门的轿子,

周围是六十名勇士,

都是以色列的精兵。

8他们个个骁勇善战,手持利剑,

腰配战刀,防备夜间的偷袭。

9所罗门王用黎巴嫩木为自己制造了一顶轿子。

10银轿柱、金靠背、紫锦坐垫,

轿子里面的装饰都是耶路撒冷少女们用爱情编织的。

11锡安的少女啊,

出去看看所罗门王的风采吧!

他头上的王冠是他母亲在他成婚那天,

在他心中欢快之日为他戴上的。

New Amharic Standard Version

ማሕልየ መሓልይ 3:1-11

1ሌሊቱን ሙሉ በዐልጋዬ ላይ ሆኜ፣

ውዴን ተመኘሁ፤

ተመኘሁት፤ ነገር ግን አላገኘሁትም።

2ተነሥቼ ወደ ከተማዪቱ እወጣለሁ፤

በዋና ዋና መንገዶችና በአደባባዮች እዘዋወራለሁ፤

ውዴንም እፈልገዋለሁ፤

ስለዚህም ፈለግሁት፤ ነገር ግን አላገኘሁትም።

3በከተማዪቱ ውስጥ ሲዘዋወሩ፣

የከተማዪቱ ጠባቂዎች አገኙኝ፤

እኔም፣ “ውዴን አይታችኋል?”

አልኋቸው።

4ከእነርሱ ጥቂት ዕልፍ እንዳልሁ፣

ውዴን አገኘሁት፤ ያዝሁት፤

ወደ እናቴ ቤት እስካመጣው፣

በማሕፀን ወደ ተሸከመችኝም ዕልፍኝ

እስካገባው ድረስ አልለቀውም።

5እናንት የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት፤

ራሱ እስኪፈልግ ድረስ፣

ፍቅርን እንዳታስነሡት ወይም እንዳትቀሰቅሱት፣

በሚዳቋና በሜዳ ዋሊያ አማጥናችኋለሁ።

6ከከርቤና ከዕጣን፣

ከነጋዴም ቅመማ ቅመም ሁሉ በተዘጋጀ ሽቱ፣

መዐዛዋ የሚያውድ፣

እንደ ጢስ ዐምድ ከምድረ በዳ የምትወጣው ይህች ማን ናት?

7እነሆ፤ የሰሎሞን ሠረገላ

በታዋቂዎቹ የእስራኤል መኳንንት፣

ስድሳ ጦረኞች ታጅባለች፤

8ሁሉም ሰይፍ የታጠቁ፣

ሁሉም በጦርነት የተፈተኑ ናቸው፤

የሌሊት አደጋን ለመከላከልም፣

እያንዳንዳቸው ሰይፋቸውን በወገባቸው ታጥቀዋል።

9ንጉሥ ሰሎሞን የራሱን ሠረገላ ሠራ፤

የሠራውም ከሊባኖስ በመጣ ዕንጨት ነው።

10ምሰሶዎቹን ከብር፣

መደገፊያውንም ከወርቅ ሠራ፤

መቀመጫውም በሐምራዊ ሐር የተሸፈነ ነው፤

ውስጡም በኢየሩሳሌም ቈነጃጅት፣

አምሮ የተለበጠ ነው።3፥10 ወይም የተለበጠውም ውስጥ፣ ከኢየሩሳሌም ቈነጃጅት የሆነ የፍቅር ስጦታ

11እናንት የጽዮን ቈነጃጅት ውጡ፤

ንጉሥ ሰሎሞን አክሊሉን ደፍቶ እዩት፤

ዘውዱም ልቡ ሐሤት ባደረገባት፣

በዚያች በሰርጉ ዕለት፣

እናቱ የደፋችለት ነው።