诗篇 88 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 88:1-18

第 88 篇

求上帝眷顾

可拉后裔的诗,就是以斯拉人希幔的训诲诗,交给乐长,调用“麻哈拉利暗俄”88:0 麻哈拉利暗俄”意为“受苦”。

1耶和华,拯救我的上帝啊,

我昼夜不停地呼求你。

2求你垂听我的祷告,

倾听我的呼求。

3我饱经患难,

生命在死亡的边缘。

4我被列在下坟墓的人中,

我的精力耗尽。

5我被扔在死人中,

如同被杀的人躺在坟墓里,

被你遗忘,不再蒙你眷顾。

6你已经把我扔在漆黑的深渊。

7你的烈怒重重地压着我,

如汹涌波涛把我淹没。(细拉)

8你使我众叛亲离,遭人唾弃。

我陷入困境,无路可逃。

9我的眼睛因哭泣而视力模糊。

耶和华啊,我天天呼求你,

举手向你呼求。

10你要行神迹给死人看吗?

死人会起来赞美你吗?(细拉)

11坟墓里的死人怎能宣扬你的慈爱呢?

灭亡的人怎能传扬你的信实呢?

12黑暗之地有谁知道你的神迹呢?

在被遗忘之地有谁知道你的公义作为呢?

13耶和华啊,我向你呼求,

我在清晨向你祷告。

14耶和华啊,你为何弃绝我?

为何掩面不理我?

15我从小受苦,几乎丧命。

你使我惊恐不已,陷入绝望。

16你的烈怒吞噬了我,

你可怕的攻击毁灭了我。

17这些灾难如洪涛整天环绕我,

彻底围住我。

18你使我的亲朋好友离我而去,

只有黑暗与我相伴。

New Amharic Standard Version

መዝሙር 88:1-18

መዝሙር 88

ሰቈቃ

ማሕሌት፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር፤ ለመዘምራን አለቃ፤ በማኸላት የሚዘመር፤ የይዝራኤላዊው የኤማን ትምህርት።

1አዳኜ የሆንህ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤

በቀንና በሌሊት በፊትህ እጮኻለሁ።

2ጸሎቴ በፊትህ ትድረስ፤

ጆሮህንም ወደ ጩኸቴ አዘንብል፤

3ነፍሴ በመከራ ተሞልታለችና፤

ሕይወቴም ወደ ሲኦል88፥3 መቃብር የሚሉ አሉ። ተቃርባለች።

4ወደ ጕድጓድ ከሚወርዱት ጋር ተቈጠርሁ፤

ዐቅምም ዐጣሁ።

5በሙታን መካከል እንደ ተጣሉ፣

ተገድለው በመቃብር ውስጥ እንደ ተጋደሙ፣

አንተ ከእንግዲህ እንደማታስባቸው፣

ከእጅህም ወጥተው እንደ ተወገዱ ሆንሁ።

6በዐዘቅት ጥልቀት ውስጥ ጣልኸኝ፤

በጨለማ ጕድጓድ ውስጥ ከተትኸኝ።

7የቍጣህ ክብደት በላዬ ዐርፏል፤

በማዕበልህም ሁሉ አጥለቅልቀኸኛል። ሴላ

8የሚቀርቡኝ ባልንጀሮቼን ከእኔ አራቅህ፤

እንዲጸየፉኝም አደረግህ፤

ተከብቤአለሁ፤ ማምለጥም አልችልም፤

9ዐይኖቼም በሐዘን ፈዘዙ።

እግዚአብሔር ሆይ፤ ዘወትር ወደ አንተ እጣራለሁ፤

እጆቼንም ወደ አንተ ዘረጋሁ።

10ድንቅ ሥራህን ለሙታን ታሳያለህን?

የሙታንስ መናፍስት ተነሥተው ያመሰግኑሃልን? ሴላ

11ምሕረትህ በመቃብር ውስጥ፣

ታማኝነትህስ እንጦርጦስ88፥11 በዕብራይስጥ አባዶን ማለት ነው፤ የመውደሚያ ስፍራ ነው። ይነገራልን?

12ድንቅ ሥራህ በጨለማ ስፍራ፣

ጽድቅህስ በመረሳት ምድር ትታወቃለችን?

13እግዚአብሔር ሆይ፤ እኔ ግን ትረዳኝ ዘንድ ወደ አንተ እጮኻለሁ፤

በጧትም ጸሎቴን በፊትህ አደርሳለሁ።

14እግዚአብሔር ሆይ፤ ለምን ታርቀኛለህ?

ፊትህንስ ከእኔ ለምን ትሰውራለህ?

15እኔ ከልጅነቴ ጀምሮ ችግረኛና ለሞት የተቃረብሁ ነበርሁ፤

መዓትህ አሠቃየኝ፤ ግራም ተጋባሁ።

16ቍጣህ በላዬ ላይ ተከነበለ፤

መዓትህም አጠፋኝ።

17ቀኑን ሙሉ እንደ ጐርፍ ከበቡኝ፤

በአንድነትም ዙሪያዬን ዐጥረው ያዙኝ።

18ወዳጄንና ባልንጀራዬን ከእኔ አራቅህ፤

ጓደኛዬ ጨለማ ብቻ ሆኖ ቀረ።