诗篇 57 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 57:1-11

第 57 篇

被围困中的呼求

大卫作的诗,交给乐长,调用“休要毁坏”。当时他因逃避扫罗躲进了洞里。

1上帝啊,求你怜悯我,怜悯我,

因为我投靠你。

我要在你翅膀下得到荫庇,

直到灾难结束。

2我向至高的上帝,

向为我成就一切的上帝呼求。

3上帝从天上施助、拯救我,

使迫害我的人蒙羞。

上帝必彰显祂的慈爱和信实。

4我被狮子包围,

躺卧在吃人的野兽中。

他们的牙齿是矛和箭,

舌头是尖刀。

5上帝啊,

愿人对你的尊崇超过诸天,

愿你的荣耀覆盖大地。

6我的仇敌设下网罗,

我心中沮丧。

他们在我走的路上挖了陷阱,

自己却掉了进去。(细拉)

7上帝啊,我心坚定,我心坚定,

我要唱诗赞美你。

8我的心啊,要振奋起来!

琴瑟啊,弹奏吧!

我要唤醒黎明!

9主啊,我要在列邦称谢你,

在列国歌颂你。

10因为你的慈爱高达诸天,

你的信实广及穹苍。

11上帝啊,

愿你得到的尊崇超过诸天,

愿你的荣耀覆盖大地。

New Amharic Standard Version

መዝሙር 57:1-11

መዝሙር 57

በጨካኝ ጠላቶች ዘንድ

57፥7-11 ተጓ ምብ – መዝ 108፥1-5

ለመዘምራን አለቃ፤ “አታጥፋ” በሚለው ቅኝት የሚዘመር፤ ከሳኦል ፊት ሸሽቶ በዋሻ በነበረበት ጊዜ፤ የዳዊት ቅኔ57 ርእሱ የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1ማረኝ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ ማረኝ፤

ነፍሴ አንተን መጠጊያ አድርጋለችና፤

በክንፎችህ ሥር እጠለላለሁ።

2ለእኔ ያሰበውን ወደሚፈጽምልኝ አምላክ፣

ወደ ልዑል እግዚአብሔር እጮኻለሁ።

3ከሰማይ ልኮ ያድነኛል፤

የረገጡኝን ያዋርዳቸዋል፤ ሴላ

እግዚአብሔር ምሕረቱንና ታማኝነቱን ይልካል።

4ነፍሴ በአንበሶች ተከብባለች፤

በሚዘነጣጥሉ አራዊት መካከል ወድቄአለሁ፤

እነዚህም፣ ጥርሳቸው ጦርና ፍላጻ፣

ምላሳቸውም የተሳለ ሰይፍ የሆኑ ሰዎች ናቸው።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤

ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትስፈን።

6ለእግሬ ወጥመድን ዘረጉ፤

ነፍሴንም አጐበጧት፤

በመተላለፊያዬ ላይ ጕድጓድ ቈፈሩ፤

ነገር ግን ራሳቸው ገቡበት። ሴላ

7እግዚአብሔር ሆይ፤ ልቤ ጽኑ ነው፤

ልቤ ጽኑ ነው፤

እቀኛለሁ፤ አዜማለሁ።

8ነፍሴ ሆይ፤ ንቂ!

በገናና መሰንቆም ተነሡ

እኔም በማለዳ እነሣለሁ።

9ጌታ ሆይ፤ በሕዝቦች መካከል አመሰግንሃለሁ፤

በሰዎችም መካከል እዘምርልሃለሁ፤

10ምሕረትህ እስከ ሰማያት ከፍ ብላለችና፤

ታማኝነትህም እስከ ደመናት ትደርሳለች።

11እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤

ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትስፈን።