诗篇 40 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 40:1-17

第 40 篇

赞美上帝之歌

大卫的诗,交给乐长。

1我曾耐心等候耶和华,

祂倾听了我的呼求。

2祂把我从绝望的深渊拉出来,

救我脱离泥泞沼泽,

把我安置在磐石上,

使我步履稳健。

3祂赐给我一首新歌,

一首赞美我们上帝的诗歌。

许多人看见便敬畏、信靠耶和华。

4信靠耶和华的人有福了!

他们不随从骄傲自大、信靠假神的人。

5我的上帝耶和华啊,

你行了许多奇事,

为我们定了许多美好的计划,

谁能与你相比!

你奇妙的作为不可胜数。

6祭物和供品非你所悦,

你开通了我的耳朵,

燔祭和赎罪祭非你所要。

7于是我说:

“看啊,我来了,

正如经卷上有关我的记载。

8我的上帝啊,

我乐意遵行你的旨意,

我铭记你的律法。”

9耶和华啊,你知道我在大会中宣扬你的公义,

没有闭口不言。

10我述说你的信实和拯救之恩,

没有把你的公义隐而不宣,

没有在大会中避而不谈你的慈爱和真理。

11耶和华啊,

求你不要收回你的怜悯,

愿你的慈爱和真理时刻守护我!

12我患难重重,罪恶缠身,

看不到出路。

我的罪过比我的头发还多,

我心惊胆战。

13耶和华啊,求你拯救我!

耶和华啊,求你快来帮助我!

14愿谋取我性命的人蒙羞受辱!

愿喜欢我被害的人狼狈逃窜!

15愿那些哈哈嘲笑我的人羞愧难当!

16愿所有寻求你的人因你而欢喜快乐!

愿渴望蒙你拯救的人时常说:

“耶和华当受尊崇!”

17我贫穷困苦,

但主眷顾我。

我的上帝啊,

你是我的帮助、我的拯救,

求你不要迟延!

New Amharic Standard Version

መዝሙር 40:1-17

መዝሙር 40

የምስጋናና የርዳታ ልመና ጸሎት

40፥13-17 ተጓ ምብ – መዝ 70፥1-5

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔርን ደጅ ጠናሁት፤

እርሱም ዘንበል አለልኝ፤ ጩኸቴንም ሰማ።

2ከሚውጥ ጕድጓድ፣

ከሚያዘቅጥ ማጥ አወጣኝ፤

እግሮቼን በዐለት ላይ አቆመ፤

አካሄዴንም አጸና።

3ለአምላካችን የሚሆን ውዳሴ፣

አዲስ ዝማሬን በአፌ ላይ አኖረ፤

ብዙዎች ያያሉ፤ ይፈራሉም፤

በእግዚአብሔር ይታመናሉ።

4እግዚአብሔርን መታመኛው ያደረገ፣

ወደ ትዕቢተኞች የማይመለከት፣

የሐሰት አማልክትን40፥4 ወይም ሐሰትን ወደሚከተሉት ተብሎ መተርጐም ይችላል። ወደሚከተሉት የማያይ

ሰው ብፁዕ ነው።

5እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤

አንተ ያደረግኸው ድንቅ ነገር ብዙ ነው፤

ለእኛ ያቀድኸውን፣

ሊዘረዝርልህ የሚችል ማንም የለም፤

ላውራው ልናገረው ብል፣

ስፍር ቍጥር አይኖረውም።

6መሥዋዕትንና ቊርባንን አልፈለግህም፤

ጆሮዎቼን ግን ከፈትህ፤40፥6 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን፣ አካልን ግን አዘጋጀህልኝ ይላል።

የሚቃጠል መሥዋዕትን፣

የኀጢአትንም መሥዋዕት አልሻህም።

7እኔም እንዲህ አልሁ፤ “እነሆ፤ መጥቻለሁ፤

ስለ እኔ በመጽሐፍ ተጽፏል፤

8አምላኬ ሆይ፤ ፈቃድህን ላደርግ እሻለሁ፤

ሕግህም በልቤ ውስጥ አለ።”

9በታላቅ ጉባኤ ውስጥ ጽድቅን አበሠርሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ እንደምታውቀው፣

ከንፈሮቼን አልገጠምሁም።

10ጽድቅህን በልቤ አልሸሸግሁም፤

ታማኝነትህንና ማዳንህን እናገራለሁ፤

ምሕረትህንና እውነትህን፣

ከታላቅ ጉባኤ አልደበቅሁም።

11እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህን አትንፈገኝ፤

ቸርነትህና እውነትህ ዘወትር ይጠብቁኝ፤

12ስፍር ቍጥር የሌለው ክፋት ከብቦኛልና፤

የኀጢአቴ ብዛት ስለ ያዘኝ ማየት ተስኖኛል፤

ከራሴ ጠጕር ይልቅ በዝቷል፤

ልቤም ከድቶኛል።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ ታድነኝ ዘንድ ፈቃድህ ይሁን፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እኔን ለመርዳት ፍጠን።

14ነፍሴን ለመንጠቅ የሚፈልጉ

ይፈሩ፤ ይዋረዱም፤

ጕዳቴንም የሚሹ፣

ተዋርደው በመጡበት ይመለሱ።

15በእኔ ላይ፣ “ዕሠይ! ዕሠይ!” የሚሉ፣

በራሳቸው ዕፍረት ይደንግጡ።

16አንተን የሚፈልጉ ሁሉ ግን፣

ሐሤት ያድርጉ፤ በአንተም ደስ ይበላቸው፤

ዘወትር የአንተን ማዳን የሚወድዱ፣

እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ይበል” ይበሉ።

17እኔ ድኻና ችግረኛ ነኝ፤

ጌታ ግን ያስብልኛል።

አንተ ረዳቴና አዳኜ ነህ፤

አምላኬ ሆይ፤ አትዘግይ።