诗篇 138 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 138:1-8

第 138 篇

感恩的祷告

大卫的诗。

1耶和华啊,

我全心全意地称谢你,

在众神明面前歌颂你。

2我要向你的圣殿下拜,

称谢你的名,

因为你是慈爱信实的,

你显明自己的尊名和应许伟大无比。

3我祷告的时候,你就应允我;

你使我刚强壮胆。

4耶和华啊,世上所有的君王听见你的话都要称谢你。

5他们要歌唱耶和华的作为,

因为耶和华荣耀无比。

6耶和华虽在高天之上,

仍看顾卑微的人,

祂对骄傲的人也了如指掌。

7耶和华啊,虽然我身陷患难,

你必保护我的性命,

伸手攻击恼怒的仇敌,

用右手拯救我。

8耶和华必成就祂为我所定的计划;

耶和华啊,你的慈爱永远长存。

求你不要撇弃你亲手所造的。

New Amharic Standard Version

መዝሙር 138:1-8

መዝሙር 138

የምስጋና መዝሙር

የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፤

በአማልክት ፊት በመዝሙር አወድስሃለሁ።

2ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ፤

ስለ ምሕረትህና ስለ ታማኝነትህ፣

ለስምህ ምስጋና አቀርባለሁ፤

ስምህንና ቃልህን፣

ከሁሉ በላይ ከፍ ከፍ አድርገሃልና።

3በጠራሁህ ቀን መልስ ሰጠኸኝ፤

ነፍሴን በማደፋፈርም ብርቱ አደረግኸኝ።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ የአፍህን ቃል በሰሙ ጊዜ፣

የምድር ነገሥታት ሁሉ ያመስግኑህ።

5የእግዚአብሔር ክብር ታላቅ ነውና፣

ስለ እግዚአብሔር መንገድ ይዘምሩ።

6እግዚአብሔር በከፍታ ስፍራ ቢሆንም፣ ዝቅ ያለውን ይመለከተዋል፤

ትዕቢተኛውን ከሩቅ ያውቀዋል።

7በመከራ መካከል ብሄድም፣

አንተ ሕይወቴን ትጠብቃታለህ፤

በጠላቶቼ ቍጣ ላይ እጅህን ትዘረጋለህ፤

በቀኝ እጅህም ታድነኛለህ።

8እግዚአብሔር በእኔ ላይ ያለውን ዐላማ ይፈጽማል፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ ለዘላለም ነው።

የእጅህንም ሥራ ቸል አትበል።