耶利米哀歌 2 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

耶利米哀歌 2:1-22

耶和华惩罚耶路撒冷

1主的怒气像乌云一样遮盖锡安2:1 ”希伯来文是“女子”,可能是对锡安的昵称,下同2:4104:22

祂使以色列的荣美从天上坠下。

祂发怒的时候并不顾念自己的脚凳。

2主毫不留情地毁灭雅各一切的住处,

祂在烈怒中夷平犹大的堡垒,

以色列及其首领蒙羞。

3祂发烈怒毁灭以色列全军。

敌人袭来时,祂收回大能的手。

祂像烈焰一样吞噬雅各

4祂抬起右手张弓搭箭,

宛若仇敌,

杀戮一切悦人眼目的人,

将祂的怒火撒向锡安城的帐篷。

5主像敌人一样毁灭以色列

吞噬她的宫殿,夷平她的堡垒,

使犹大人哀哭不止。

6祂摧毁自己的居所,

如同摧毁花园;

祂摧毁自己规定的聚会之处,

使锡安的人民忘记安息日和节期。

祂在烈怒中弃绝所有的君王和祭司。

7主撇弃自己的祭坛,

憎恶自己的圣所,

耶路撒冷的殿墙交给敌人。

他们像过节一样,

在耶和华的殿中喧嚷吵闹。

8耶和华决意拆毁锡安的城墙,

祂拉了准线,

定意毁灭,决不停止。

祂使城墙和壁垒一同悲哀哭泣。

9锡安的城门陷入地中,

主摧毁、砍断她的门闩。

她的君王和首领流落异乡,

律法不复存在,

她的先知得不到从耶和华而来的异象。

10锡安城的长老腰束麻布,

头蒙灰尘,坐在地上,

默然不语;

耶路撒冷的少女垂头至地。

11我哭得眼睛失明,

心如刀割,肝胆欲碎,

因为人民惨遭毁灭,

儿童和婴孩昏倒在街头。

12孩子们问母亲:

“哪里有饼和酒呢?”

他们像受伤的勇士,

昏倒在城中的街头,

在母亲怀中奄奄一息。

13耶路撒冷啊,我该说什么呢?

谁能与你的苦难相比呢?

锡安啊,我用什么话语才能安慰你呢?

你的伤口深如海洋,

谁能医治你呢?

14你的先知所见的异象虚假无用。

他们没有揭露你的罪恶,

以致你被掳。

他们给你的预言虚假谬误。

15路人都拍掌嘲笑你。

他们向耶路撒冷城摇头,

嗤笑道:

“这就是那被誉为完美无瑕、

普世喜悦的城吗?”

16敌人都幸灾乐祸地讥讽你,

他们咬牙切齿地说:

“我们吞灭了她!

这是我们期待已久的日子!

我们终于见到这一天了!”

17耶和华实现了祂的计划,

成就了祂很久以前的应许。

祂毫不留情地毁灭了你,

使你的仇敌幸灾乐祸,

耀武扬威。

18锡安的城墙啊,

你要从心里向主呼求!

你的眼泪要像江河一样昼夜涌流,

不歇不眠。

19你要在夜间起来,

在主面前整夜呼求,

向祂倾心吐意;

你要为饿昏街头的孩童向主举手祷告。

20“耶和华啊,求你看看,

你曾这样对付过谁呢?

母亲岂能吃自己的孩子?

祭司和先知岂能在主的圣所中被杀?

21“老人和小孩陈尸街头,

少男少女都丧身刀下。

你在发怒的日子杀了他们,

毫不留情。

22“你从四面八方召人攻击我,

如同召集人过节。

耶和华发怒的日子,

无人得以逃脱,无人得以幸免。

敌人杀光了我养育的孩子。”

New Amharic Standard Version

ሰቈቃወ 2:1-22

א አሌፍ

2 ይህ ምዕራፍ ጥቅሶቹ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀምር፣ የመጀመሪያው ወይም የመጨረሻው መሥመር ትርጕም የሚሰጥ ቃል ወይም ዐረፍተ ነገር ያለው ግጥም ነው። 1ጌታ የጽዮንን ሴት ልጅ፣

በቍጣው ደመና እንዴት ጋረዳት!2፥1 ወይም እግዚአብሔር በቍጣው የጽዮንን ሴት ልጅ እንዴት አዋረዳት!

ከሰማይ ወደ ምድር፣

የእስራኤልን ክብር ወርውሮ ጣለው፤

በቍጣው ቀን፣

የእግሩን መቀመጫ አላስታወሰም።

ב ቤት

2የያዕቆብን መኖሪያ ሁሉ፣

ጌታ ያለ ርኅራኄ ዋጣቸው፤

የይሁዳን ሴት ልጅ ምሽጎች፣

በቍጣው አፈረሳቸው፤

መንግሥቷንና መሳፍንቷን፣

በማዋረድ ወደ ምድር ጣላቸው።

ג ጊሜል

3በጽኑ ቍጣው፣

የእስራኤልን ቀንድ ሁሉ2፥3 ወይም ብርታትን ሁሉ፤ ወይም ንጉሥ ሁሉ፤ ቀንድ በዚህ ቦታ ብርታትን ያመለክታል። ሰበረ፤

ጠላት በተቃረበ ጊዜ፣

ቀኝ እጁን ወደ ኋላ መለሰ፤

በዙሪያው ያለውን ሁሉ እንደሚበላ እሳት፣

በያዕቆብ ላይ የእሳት ነበልባል ነደደ።

ד ዳሌት

4እንደ ጠላት ቀስቱን ገተረ፤

ቀኝ እጁ ተዘጋጅታለች፤

ለዐይን ደስ የሚያሰኙትን ሁሉ፤

እንደ ጠላት ዐረዳቸው፤

በጽዮን ሴት ልጅ ድንኳን ላይ፣

ቍጣውን እንደ እሳት አፈሰሰ።

ה ሄ

5ጌታ እንደ ጠላት ሆነ፤

እስራኤልንም ዋጠ፤

ቤተ መንግሥቶቿን ሁሉ ዋጠ፤

ምሽጎቿን አፈራረሰ፤

በይሁዳ ሴት ልጅ፣

ልቅሶንና ሰቈቃን አበዛ።

ו ዋው

6ማደሪያውን እንደ አትክልት ስፍራ ባዶ አደረገ፤

መሰብሰቢያ ስፍራውን አፈረሰ፤

እግዚአብሔር ጽዮንን፣

ዓመት በዓላቶቿንና ሰንበታቷን እንድትረሳ አደረጋት፤

በጽኑ ቍጣው፣

ንጉሡንና ካህኑን እጅግ ናቀ።

ז ዛይን

7ጌታ መሠዊያውን ናቀ፤

መቅደሱንም ተወ፤

የቤተ መንግሥቶቿን ቅጥሮች፣

ለጠላት አሳልፎ ሰጠ፤

በዓመት በዓል ቀን እንደሚደረገው

በእግዚአብሔር ቤት በኀይል ጮኹ።

ח ኼት

8በጽዮን ሴት ልጅ ዙሪያ ያለውን ቅጥር፣

እግዚአብሔር ለማፍረስ ወሰነ፤

የመለኪያ ገመድ ዘረጋ፤

ከማጥፋትም እጆቹን አልሰበሰበም፤

ምሽጎችና ቅጥሮች እንዲያለቅሱ አደረገ፤

በአንድነትም ጠፉ።

ט ቴት

9በሮቿ ወደ ምድር ሰመጡ፤

የብረት መወርወሪያዎቻቸውን ሰባበረ፤ አጠፋቸውም፤

ንጉሧና መሳፍንቷ በአሕዛብ መካከል ተማርከው ተሰድደዋል፤

ሕጉ ከእንግዲህ አይኖርም፤

ነቢያቷም ከእንግዲህ፣

ከእግዚአብሔር ራእይ አያገኙም።

י ዮድ

10የጽዮን ሴት ልጅ ሽማግሌዎች፣

በምድር ላይ በዝምታ ተቀምጠዋል፤

በራሳቸው ላይ ትቢያ ነሰነሱ፤

ማቅም ለበሱ፤

የኢየሩሳሌም ወጣት ሴቶች፣

ራሳቸውን ወደ ምድር ዝቅ አደረጉ።

כ ካፍ

11ዐይኔ በልቅሶ ደከመ፤

ነፍሴ በውስጤ ተሠቃየች፤

ልቤም በሐዘን ፈሰሰች፣

በከተማዪቱ መንገዶች ላይ፣

ሕዝቤ ተደምስሰዋልና፤

ልጆችና ሕፃናት ደክመዋልና።

ל ላሜድ

12በከተማዪቱ መንገዶች ላይ፣

እንደ ቈሰሉ ሰዎች ሲደክሙ፣

በእናታቸው ክንድ ላይ፣

ነፍሳቸው በመውጣት ላይ ሳለች፣

“እንጀራና የወይን ጠጅ የት አለ?”

እያሉ እናቶቻቸውን ይጠይቃሉ።

מ ሜም

13የኢየሩሳሌም ሴት ልጅ ሆይ፤ ስላንቺ ምን ማለት እችላለሁ?

ከምንስ ጋር አወዳድርሻለሁ? ድንግሊቱ የጽዮን ልጅ ሆይ፤

አጽናናሽ ዘንድ፣

በምን ልመስልሽ እችላለሁ?

ቍስልሽ እንደ ባሕር ጥልቅ ነው፤

ማንስ ሊፈውስሽ ይችላል?

נ ኑን

14የነቢያቶችሽ ራእይ፣

ሐሰትና ከንቱ ነው፤

ምርኮኛነትሽን ለማስቀረት፣

ኀጢአትሽን አይገልጡም።

የሚሰጡሽም የትንቢት ቃል፣

የሚያሳስትና ከመንገድ የሚያወጣ ነው።

ס ሳሜክ

15በአጠገብሽ የሚያልፉ ሁሉ፣

እጃቸውን ያጨበጭቡብሻል፤

“የውበት መደምደሚያ፣ የምድር ሁሉ ደስታ፣

የተባለች ከተማ ይህች ናትን?”

እያሉ ራሳቸውን በመነቅነቅ፣

በኢየሩሳሌም ሴት ልጅ ላይ ያሾፋሉ።

ע ዐዪን

16ጠላቶችሽ ሁሉ በአንድ ላይ፣

አፋቸውን በኀይል ከፈቱ፤

ጥርሳቸውን እያፏጩ አሾፉ፤

እንዲህም አሉ፤ “ውጠናታል፤

የናፈቅነው ጊዜ ይህ ነበር፤

ኖረንም ልናየው በቃን።”

פ ፌ

17እግዚአብሔር ያሰበውን አደረገ፤

ከረዥም ጊዜ በፊት የተናገረውን፣

ቃሉን ፈጸመ፤

ያለ ርኅራኄ አፈረሰሽ፤

ጠላት በሥቃይሽ ላይ እንዲደሰት፣

የጠላትሽንም ቀንድ2፥17 ቀንድ በዚህ ቦታ ብርታትን ያመለክታል ከፍ ከፍ አደረገ።

צ ጻዲ

18የሕዝቡ ልብ፣ ወደ ጌታ ጮኸ።

የጽዮን ሴት ልጅ ቅጥር ሆይ፤

ቀንና ሌሊት፣

እንባሽ እንደ ወንዝ ይፍሰስ፤

ለራስሽ ዕረፍትን አትስጪ፣

ዐይኖችሽ ከማንባት አያቋርጡ።

ק ቆፍ

19የሌሊቱ ሰዓት ሲጀምር፣

ተነሺ በሌሊት ጩኺ፤

በጌታ ፊት፣

ልብሽን እንደ ውሃ አፍስሺ፤

በየመንገዱ ዳር ላይ፣ በራብ ስለወደቁት፣

ስለ ልጆችሽ ሕይወት፣ እጆችሽን ወደ እርሱ አንሺ።

ר ሬሽ

20አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ እይ፤ ተመልከትም፤

በማን ላይ እንዲህ አድርገህ ታውቃለህ?

በውኑ እናቶች ሕፃኖቻቸውን፣

ተንከባክበው ያሳደጓቸውን ልጆች ይብሉን?

ካህኑና ነቢዩስ፣

በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ ይገደሉን?

ש ሲን እና ሺን

21በየመንገዱ ዐቧራ ላይ፣

ወጣትና ሽማግሌ በአንድነት ወደቁ፤

ወይዛዝርቴና ጐበዛዝቴ፣

በሰይፍ ተገደሉ፤

በቍጣህ ቀን ገደልሃቸው፤

ያለ ርኅራኄም ዐረድሃቸው።

ת ታው

22“በበዓል ቀን ለግብዣ እንደምትጠራ፣

ሽብርን ከየአቅጣጫው በእኔ ላይ ጠራህ፤

በእግዚአብሔር የቍጣ ቀን፣

ማንም አላመለጠም ወይም አልተረፈም፤

የተንከባከብኋቸውንና ያሳደግኋቸውን፣

ጠላቴ አጠፋብኝ።”