耶利米书 41 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

耶利米书 41:1-18

基大利被杀

1七月,王室宗亲、犹大王的大臣、以利沙玛的孙子、尼探雅的儿子以实玛利带着十个人去米斯巴亚希甘的儿子基大利。趁在米斯巴一同吃饭的时候, 2尼探雅的儿子以实玛利和同来的十个人突然起来拔刀杀了巴比伦王委任管理犹大沙番的孙子、亚希甘的儿子基大利3还杀了所有在米斯巴基大利在一起的犹大人和那里的迦勒底士兵。

4第二天,基大利被杀的事仍无人知道。 5当天,从示剑示罗撒玛利亚来了八十个人,他们剃了胡须,撕裂衣服,割破身体,手里拿着素祭和乳香要去耶和华的殿。 6以实玛利就从米斯巴出来迎接他们,边走边哭,见面后邀请他们去见亚希甘的儿子基大利7到了城中,以实玛利和部下便屠杀他们,弃尸于蓄水池中。 8其中有十个人对以实玛利说:“请不要杀我们,我们在田野里藏了许多大麦、小麦、油和蜜。”他就没有杀他们。 9以实玛利抛尸的地方是个很大的蓄水池,是从前亚撒王为抵御以色列巴沙而修建的。尼探雅的儿子以实玛利用被杀者的尸体填满了蓄水池。 10以实玛利还掳去了留在米斯巴的公主和其他人。护卫长尼布撒拉旦曾委任亚希甘的儿子基大利管理这些人。尼探雅的儿子以实玛利带着俘虏前往亚扪

11加利亚的儿子约哈难和其他将领听说尼探雅的儿子以实玛利的所作所为, 12便率领部下去攻打他,在基遍的大水池边追上了他。 13-14以实玛利米斯巴掳走的人看见约哈难和众将领,喜出望外,都转身投奔约哈难15尼探雅的儿子以实玛利带着八个人逃脱约哈难的追击,前往亚扪16加利亚的儿子约哈难和众将领从基遍救回了那些被掳走的士兵、妇孺和宫廷侍臣。 17他们启程前往埃及,途中在伯利恒附近的基罗特金罕住下。 18他们是害怕迦勒底人才逃往埃及的,因为尼探雅的儿子以实玛利杀了巴比伦王委任管理犹大亚希甘的儿子基大利

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 41:1-18

1ከንጉሣዊ ቤተ ሰብ የሆነው ከንጉሡ የጦር መኰንንኖች አንዱ የነበረው የኤሊሳማ ልጅ የናታንያ ልጅ እስማኤል፣ በሰባተኛው ወር ከዐሥር ሰዎች ጋር ወደ ምጽጳ ወደ አኪቃም ልጅ ወደ ጎዶልያስ መጣ፤ በዚያም በአንድነት ሊበሉ በማእድ ተቀምጠው ሳለ፣ 2የናታንያ ልጅ እስማኤልና አብረውት የነበሩ ዐሥሩ ሰዎች ተነሥተው፣ የባቢሎን ንጉሥ በምድሪቱ ላይ ገዥ አድርጎ የሾመውን የሳፋንን ልጅ የአኪቃምን ልጅ ጎዶልያስን በሰይፍ መቱት፤ ገደሉትም። 3ደግሞም እስማኤል በምጽጳ ከጎዶልያስ ጋር የነበሩትን አይሁድ ሁሉ፣ በዚያም የተገኙትን የባቢሎን41፥3 ወይም የከለዳውያን ወታደሮች ገደላቸው።

4ጎዶልያስ በተገደለ ማግስት፣ ማንም ስለ ሁኔታው ከማወቁ በፊት፣ 5ሰማንያ ሰዎች ጢማቸውን ተላጭተው፣ ልብሳቸውን ቀድደው፣ ገላቸውን ነጭተው የእህል ቍርባንና ዕጣን በመያዝ ከሴኬም፣ ከሴሎና ከሰማርያ ወደ እግዚአብሔር ቤት ለማቅረብ መጡ። 6የናታንያ ልጅ እስማኤል ሊገናኛቸው እያለቀሰ ከምጽጳ ወጣ፤ ሲያገኛቸውም፣ “ወደ አኪቃም ልጅ ወደ ጎዶልያስ ኑ” አላቸው። 7ወደ ከተማዪቱ በገቡ ጊዜ፣ የናታንያ ልጅ እስማኤልና አብረውት የነበሩ ሰዎች ዐረዷቸው፤ በውሃ ማጠራቀሚያ ጕድጓድ ውስጥም ጣሏቸው። 8ከተገደሉት ጋር የነበሩ ዐሥር ሰዎች ግን እስማኤልን፣ “እባክህ አትግደለን! በዕርሻችን ውስጥ የሸሸግነው ስንዴና ገብስ፣ የወይራ ዘይትና ማር ስላለን እባክህን አትግደለን” አሉት። እርሱም ተዋቸው፤ ከሌሎቹም ጋር አልገደላቸውም። 9እስማኤል ከጎዶልያስ በተጨማሪ የገደላቸው ሰዎች ሁሉ ሬሳ የተጣለበት የውሃ ማጠራቀሚያ ጕድጓድ፣ ንጉሡ አሳ የእስራኤልን ንጉሥ ባኦስን ስለ ፈራ ለመከላከል ያሠራው ነበር፤ ይህን ጕድጓድ የናታንያ ልጅ እስማኤል በሬሳ ሞላው።

10እስማኤል በምጽጳ የቀረውን ሕዝብ ሁሉ ምርኮኛ አደረገ፤ እነርሱም የባቢሎን የክብር ዘበኞች አዛዥ ናቡረዘረዳን የአኪቃምን ልጅ ጎዶልያስን በላያቸው ገዥ አድርጎ የሾመባቸው የንጉሡ ሴቶች ልጆችና በዚያ የቀሩት ሌሎች ሰዎች ሁሉ ነበሩ። የናታንያ ልጅ እስማኤል እነዚህን ማርኮ ወደ አሞናውያን ለመሻገር ተነሣ።

11የቃሬያ ልጅ ዮሐናና ከእርሱ ጋር የነበሩት የጦር መኰንኖች ሁሉ የናታንያ ልጅ እስማኤል የፈጸመውን ግፍ ሁሉ በሰሙ ጊዜ፣ 12የናታንያን ልጅ እስማኤልን ሊወጉ ሰዎቻቸውን ሁሉ ይዘው ሄዱ፤ በገባዖንም ባለው በታላቁ ኵሬ አጠገብ ደረሱበት። 13እስማኤል የያዛቸው ሰዎች ሁሉ የቃሬያን ልጅ ዮሐናንንና አብረውት የነበሩትን የጦር መኰንኖች ባዩ ጊዜ ደስ አላቸው። 14እስማኤል ከምጽጳ ማርኮ የወሰዳቸው ሰዎች ሁሉ አምልጠው ወደ ቃሬያ ልጅ ወደ ዮሐናን ገቡ። 15የናታንያ ልጅ እስማኤል ግን አብረውት ከነበሩት ስምንት ሰዎች ጋር ከዮሐናን አመለጠ፤ ሸሽቶም ወደ አሞናውያን ገባ።

ሽሽት ወደ ግብፅ

16የቃሬያ ልጅ ዮሐናንና ከእርሱ ጋር የነበሩት የጦር መኰንንኖች ሁሉ የናታንያ ልጅ እስማኤል የአኪቃምን ልጅ ጎዶልያስን ከገደለ በኋላ፣ በምጽጳ ከማረካቸው የተረፉትን ሰዎች በማስመለስ ይዘው ሄዱ፤ እነዚህም፣ ወታደሮች፣ ሴቶች ሕፃናትና ከገባዖን ያመጧቸው የቤተ መንግሥት ባለ ሥልጣኖች ነበሩ። 17ከዚያም ተነሥተው ሄዱ፤ ወደ ግብፅም በማምራት በቤተ ልሔም አጠገብ ባለችው በጌሮት ከመዓም ዐረፉ፤ 18ወደ ግብፅም የሄዱት ከባቢሎናውያን41፥18 ወይም ከከለዳውያን ለማምለጥ ነበር፤ ባቢሎናውያንንም የፈሩት የናታንያ ልጅ እስማኤል የባቢሎን ንጉሥ የምድሪቱ ገዥ አድርጎ የሾመውን የአኪቃምን ልጅ ጎዶልያስን በመግደሉ ነው።