耶利米书 33 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

耶利米书 33:1-26

应许以色列人必复兴

1耶利米被囚禁在护卫兵院子里的时候,耶和华第二次对他说: 2“耶和华创造大地,使其成形、根基稳固,祂名叫耶和华。祂说, 3‘你呼求我,我就回应你,并且把你不知道的伟大、奥妙之事告诉你。 4以色列的上帝耶和华说,耶路撒冷城中的房屋和王宫被拆毁,用来修建防卫工事, 5城中的人与迦勒底人争战只会使自己的房屋堆满死尸,因为我要在愤怒中毁灭他们。他们作恶多端,我必掩面不理这城。 6但有一天,我必使这城复兴,医治她的创伤,使她繁荣昌盛。 7我要使被掳的犹大人和以色列人回到故土,重建家园。 8我要除去他们的一切罪恶,赦免他们的一切罪过。 9这城要使我在天下万国面前得到尊崇、颂赞和荣耀。万民听见我使这城繁荣昌盛,都恐惧战栗。’”

10耶和华说:“你们说犹大的城邑和耶路撒冷的街道一片荒凉、人畜绝迹, 11但这些地方必传出欢乐声、新郎新娘的欢笑声和在耶和华殿中献感恩祭者的歌唱声,

“‘要感谢万军之耶和华,

因为耶和华是美善的,

祂的慈爱永远长存’。

因为我必使被掳的人回到故土,重建家园。这是耶和华说的。”

12万军之耶和华说:“在这一片荒凉、人畜绝迹的地方,在它所有城邑的周围必再有供牧人放羊的草场。 13在山区、丘陵和南地的城邑,以及便雅悯耶路撒冷周围和犹大的城邑必有人清点羊群。这是耶和华说的。” 14耶和华说:“看啊,时候将到,我要实现我给以色列人和犹大人的美好应许。 15那时,我要使大卫公义的苗裔兴起,他要在地上秉公行义。 16那时,犹大必得到拯救,耶路撒冷必安享太平并被称为‘耶和华是我们的义’。 17因为耶和华说,‘我应许大卫的后裔必永远统治以色列18做祭司的利未人必永远在我面前献燔祭、素祭等祭物。’”

19耶和华对耶利米说: 20“这是耶和华说的,‘除非你们能废除我与白昼黑夜所立的约,叫白昼黑夜不再按时更替, 21才能废除我与我仆人大卫所立的约,使他的王位后继无人,也才能废除我与事奉我的利未祭司所立的约。 22我要使我仆人大卫的后裔和事奉我的利未人像天上的星和海边的沙一样不可胜数。’”

23耶和华对耶利米说: 24“你听见了吗?人们说,‘耶和华已经弃绝了祂所拣选的以色列犹大两个国家。’他们藐视我的子民,视他们为亡国之民。 25然而,耶和华说,‘正如我决不废弃我所定的昼夜交替和天地运行之律, 26我也决不弃绝雅各的后裔,不弃绝我仆人大卫的后裔。我必让大卫的后裔做王统治亚伯拉罕以撒雅各的子孙,因为我必使被掳的人回到故土,恩待他们。’”

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 33:1-26

የመመለስ ተስፋ

1ኤርምያስ በዘብ ጠባቂዎች አደባባይ በግዞት ሳለ፣ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ዳግመኛ ወደ እርሱ መጣ፤ 2“ምድርን የፈጠራት፣ ያበጃትና የመሠረታት እግዚአብሔር፣ ስሙ እግዚአብሔር የሆነ፣ እርሱ እንዲህ ይላል፤ 3‘ወደ እኔ ጩኽ፤ እኔም እመልስልሃለሁ፤ አንተም የማታውቀውን ታላቅና የማይመረመር ነገር እገልጥልሃለሁ።’ 4የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ከባቢሎናውያን33፥4 ወይም ከለዳውያን ጋር ባለው ውጊያ፣ ዐፈር በመደልደልና በሰይፍ የሚደረገውን ጥቃት ለመከላከል ስለ ፈረሱት ስለዚህች ከተማ ቤቶችና ስለ ይሁዳ ነገሥታት ቤተ መንግሥት እንዲህ ይላል፤ 5‘እነዚህ በቍጣዬና በመዓቴ በምገድላቸው ሰዎች ሬሳ ይሞላሉ፤ ስለ ክፋቷ ሁሉ ከዚህች ከተማ ፊቴን እሰውራለሁ።

6“ ‘ይሁን እንጂ፣ ፈውስንና ጤንነትን እንደ ገና እሰጣታለሁ፤ ሕዝቤንም እፈውሳለሁ፤ በብዙ ሰላምና በርጋታ እንዲኖሩ አደርጋለሁ። 7የይሁዳን ምርኮና የእስራኤልን ምርኮ እመልሳለሁ፤33፥7 ወይም ይሁዳንና እስራኤልን ከምርኮ እመልሳለሁ ቀድሞ እንደ ነበሩት ሁኔታ አድርጌ አበጃቸዋለሁ፤ 8እኔን ከበደሉበት ኀጢአት ሁሉ አነጻቸዋለሁ፤ በእኔ ላይ ያመፁበትንም ኀጢአታቸውን ሁሉ ይቅር እላለሁ። 9ይህች ከተማ፣ ለእርሷ ያደረግሁትን በጎ ነገር ሁሉ በሚሰሙት የምድር ሕዝቦች ሁሉ ፊት ለዝና፣ ለደስታ፣ ለምስጋናና ለክብር ትሆናለች፤ ከምሰጣትም የተትረፈረፈ ብልጽግናና ሰላም የተነሣ ይፈራሉ፤ ይንቀጠቀጣሉም።’

10እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ይህችን ስፍራ፣ “ሰውና እንስሳት የማይኖሩባት ባድማ ናት” ትላላችሁ፤ ነገር ግን ሰውም ሆነ እንስሳ ባልነበሩባቸውና ባድማ በሆኑት በይሁዳ ከተሞችና በኢየሩሳሌም መንገዶች፣ እንደ ገና ድምፅ ይሰማል፤ 11የሐሤትና የደስታ ድምፅ፣ የሙሽራውና የሙሽራዪቱ ድምፅ፣ እንዲሁም፣

“ ‘ “እግዚአብሔር ቸር ነውና፤

ምሕረቱም ለዘላለም ነውና፤

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርን አመስግኑ፤”

የሚል የምስጋናን መሥዋዕት ይዘው ወደ እግዚአብሔር ቤት የሚመጡ ሰዎች ድምፅ ይሰማል፤ የምድሪቱን ምርኮ ቀድሞ እንደ ነበረ እመልሳለሁና፤’ ይላል እግዚአብሔር

12“የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ሰውም ሆነ እንስሳት በማይኖሩበት በዚህ ባዶ ስፍራ፣ በከተማዎቹም ሁሉ እረኞች መንጎቻቸውን የሚያሳርፉበት እንደ ገና ያገኛሉ። 13በተራራማው አገር፣ በምዕራብ ተራሮች ግርጌና በኔጌብ ባሉ ከተሞች በብንያም አገር፣ በይሁዳ ከተሞች እንዲሁም በኢየሩሳሌም ዙሪያ ባሉ መንደሮች መንጎች እንደ ገና በሚቈጥራቸው ሰው እጅ ሥር ያልፋሉ’ ይላል እግዚአብሔር

14“ ‘ለእስራኤል ቤትና ለይሁዳ ቤት የገባሁትን የተስፋ ቃል የምፈጽምበት ጊዜ ይመጣል’ ይላል እግዚአብሔር

15“ ‘በዚያ ዘመንና በዚያ ጊዜ፣

ከዳዊት ቤት ጻድቅ ቅርንጫፍ አበቅላለሁ፤

በምድሪቱም ፍትሕንና ጽድቅን ያደርጋል።

16በዚያ ዘመን ይሁዳ ይድናል፤

ኢየሩሳሌም በሰላም ትኖራለች፤

የምትጠራበትም ስም፣

እግዚአብሔር ጽድቃችን”

የሚል ይሆናል።’ 17እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ ‘ከዳዊት ዘር በእስራኤል ቤት ዙፋን ላይ የሚቀመጥ ሰው ፈጽሞ አይታጣም፤ 18ሌዋውያን ከሆኑት ካህናትም የሚቃጠል መሥዋዕት ለማቅረብ፣ የእህል ቍርባን ለማቃጠልና ሌላውንም መሥዋዕት ለመሠዋት ሁልጊዜ በፊቴ የሚቆም ሰው አይታጣም።’ ”

19የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ እንዲህ ሲል መጣ፤ 20እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ለቀንና ለሌሊት የወሰንሁትን ሥርዐት በማፋለስ ቀንና ሌሊት በተወሰነላቸው ጊዜ እንዳይፈራረቁ ኪዳኔን ማፍረስ ብትችሉ፣ 21በዚያ ጊዜ ከአገልጋዬ ከዳዊት ጋር የገባሁትን ኪዳን፣ እንዲሁም በፊቴ በክህነት ከሚያገለግሉት ሌዋውያን ጋር የገባሁትን ኪዳን ማፍረስ ይቻላል፤ ዳዊትም ከእንግዲህ በዙፋኑ ላይ የሚነግሥ ዘር አይኖረውም። 22የአገልጋዬን የዳዊትን ዘር እንዲሁም በፊቴ የሚቆሙትን ሌዋውያን እንደማይቈጠሩ እንደ ሰማይ ከዋክብትና እንደማይሰፈር የባሕር አሸዋ አበዛቸዋለሁ።’ ”

23የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ እንዲህ ሲል መጣ፤ 24“ይህ ሕዝብ፣ ‘እግዚአብሔር የመረጣቸውን ሁለቱን መንግሥታት33፥24 ወይም ወገን ጥሏል’ እንደሚሉ አላስተዋልህምን? ሕዝቤን ንቀዋል፤ እንደ ሕዝብም አልቈጠሯቸውም። 25እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘የቀንና የሌሊት ኪዳኔን፣ የሰማይንና የምድርንም ሥርዐት ያጸናሁ እኔ ካልሆንሁ፣ 26የያዕቆብንና የአገልጋዬን የዳዊትን ዘር እጥላለሁ፤ ከልጆቹም በአብርሃም፣ በይስሐቅና በያዕቆብ ዘር ላይ ገዥ እንዲሆኑ አልመርጥም፤ ይህንም የምለው ምርኳቸውን ስለምመልስና33፥26 ወይም ከምርኮ እመልሳቸዋለሁ ስለምራራላቸው ነው።’ ”