耶利米书 22 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

耶利米书 22:1-30

警告犹大的王

1耶和华对我说:“你下到犹大王的宫殿,这样宣告, 2‘坐在大卫宝座上的犹大王啊,你和你的臣仆以及进出这城门的百姓都要听耶和华的话。 3耶和华说,你们为人要公义正直,要从欺压者手中解救受剥削的人。不要欺凌、虐待异乡人和孤儿寡妇,不可在这地方滥杀无辜。 4如果你们遵守我的命令,大卫的子孙必继续做王,并乘车、骑马率领臣民进出王宫。 5但如果你们不遵守我的命令,我凭自己起誓,这王宫必沦为废墟。这是耶和华说的。’”

6论到犹大王的宫殿,耶和华说:

“虽然它在我眼中美如基列

又像黎巴嫩的山峰,

但我必使它变成不毛之地,

变成杳无人烟的城邑。

7我要派人拿着兵器来摧毁它,

他们要砍下它最好的香柏木,

扔进火里。

8“各国的人经过这城时都会彼此议论说,‘为什么耶和华这样对待这座大城?’ 9有人会回答,‘因为城里的人背弃了他们的上帝耶和华的约,供奉、祭拜其他神明。’”

10你们不要为死去的王哀哭,

要为被掳走的王哀哭,

因为他必一去不返,

再也看不到自己的家园。

11论到接替父亲约西亚犹大王、后来被掳走的沙龙22:11 沙龙”也叫“约哈斯”。,耶和华说:“他必一去不返, 12客死异乡,永别故土。”

对约雅敬的审判

13耶和华说:

约西亚的儿子犹大约雅敬啊,你有祸了!

你以不公不义的手段建造宫廷殿宇,

不给工人发工钱。

14你说要为自己建造宏伟的宫殿、宽敞的房间。

你安上窗户,

镶上香柏木,

涂上红漆。

15难道你大肆使用香柏木就能显出你做王的气派吗?

你父亲也吃也喝,

但他秉公行义,

所以他凡事顺利;

16他为困苦和贫穷的人申冤,

所以他凡事顺利。

这才是真正认识我。

这是耶和华说的。

17可是,你一心贪图不义之财,

滥杀无辜,横征暴敛。”

18因此,论到犹大约西亚的儿子约雅敬,耶和华说:

“没有人会为他哀悼说,

‘唉,我的弟兄啊!

唉,我的姊妹啊!’

没有人会为他哀悼说,

‘唉,主人啊!

唉,他的尊荣!’

19你必像死驴一样被拖到耶路撒冷的城门外,暴尸荒野。”

对耶路撒冷的警告

20耶路撒冷人啊,

你们要上黎巴嫩大声哭喊,

巴珊哀号,

亚巴琳痛哭,

因为你们的盟友被消灭了。

21在你们兴盛的时候,

我曾警告过你们,

你们却不听。

你们从小就叛逆,

不听我的话。

22你们的首领都要被风卷去,

你们的盟友都要被掳走,

你们必因自己的恶行而蒙羞受辱。

23住在黎巴嫩、安居在香柏木宫殿中的人啊,

当妇人分娩般的痛苦临到你们的时候,

你们将怎样呻吟呢!”

对哥尼雅的审判

24耶和华说:“犹大约雅敬的儿子哥尼雅22:24 哥尼雅”即“耶哥尼雅”,又叫“约雅斤”。啊,我凭我的永恒起誓,即使你是我右手上盖章的戒指,我也要把你摘下来, 25交给那些想杀你的人,交给你所惧怕的人,就是巴比伦尼布甲尼撒和他的迦勒底军队。 26我要把你和你母亲赶到异乡,那里不是你们的出生之地,却是葬身之处。 27你们渴望回到故乡,却不能如愿以偿。”

28难道哥尼雅是个被人鄙视、无人理睬的破瓶子吗?

为什么他和他的子孙被赶到陌生之地?

29大地啊,大地啊,大地啊,

要听耶和华的话!

30耶和华说:

“你要把这人作为无儿无女、

一生失败的人记录下来,

因为他的后裔中无一人能成功地继承大卫的宝座,

统治犹大。”

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 22:1-30

በክፉዎች ነገሥታት ላይ የተሰጠ ፍርድ

1እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ወደ ይሁዳ ንጉሥ ቤተ መንግሥት ውረድ፤ ይህንም መልእክት በዚያ እንዲህ ብለህ ተናገር፤ 2‘በዳዊት ዙፋን የተቀመጥህ፣ የይሁዳ ንጉሥ ሆይ፤ አንተና መኳንንትህ፣ በእነዚህም በሮች የሚገባ ሕዝብህ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ። 3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ፍትሕንና ጽድቅን አድርጉ፤ የተበዘበዘውን ከጨቋኙ እጅ አድኑት፤ መጻተኛውን፣ ወላጅ የሌለውንና መበለቲቱን አትበድሉ፤ አትግፏቸውም፤ በዚህም ስፍራ ንጹሕ ደም አታፍስሱ። 4እነዚህን ትእዛዞች በሚገባ ብትጠብቁ፣ በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጡ ነገሥታት፣ ከመኳንንታቸውና ከሕዝባቸው ጋር በሠረገሎችና በፈረሶች ተቀምጠው በዚህ ቤተ መንግሥት በሮች ይገባሉ፤ ይወጣሉም። 5ነገር ግን እነዚህን ትእዛዞች ባትጠብቁ፣ ይህ ቤተ መንግሥት እንዲወድም በራሴ ምያለሁ፤” ይላል እግዚአብሔር።’ ”

6ስለዚህ እግዚአብሔር ስለ ይሁዳ ንጉሥ ቤተ መንግሥት እንዲህ ይላል፤

“አንተ ለእኔ እንደ ገለዓድ፣

እንደ ሊባኖስ ተራራ ጫፍ ውብ ብትሆንም፣

በርግጥ እንደ ምድረ በዳ፣

ሰው እንደማይኖርባቸው ከተሞች አደርግሃለሁ።

7በነፍስ ወከፍ መሣሪያ የሚይዙትን፣

አጥፊዎችን በአንተ ላይ አዘጋጃለሁ።

ምርጥ የዝግባ ዛፎችን ይቈርጣሉ፤

ወደ እሳትም ይጥሏቸዋል።

8“ከተለያየ አገር የመጡ ሕዝቦች በዚህች ከተማ በኩል ሲያልፉ፣ ‘እግዚአብሔር በዚህች ታላቅ ከተማ ላይ ለምን እንዲህ አደረገ?’ እያሉ እርስ በርስ ይነጋገራሉ፤ 9ከዚያም፣ ‘የአምላካቸውን የእግዚአብሔርን ኪዳን ትተው ሌሎችን አማልክት ስላመለኩና ስላገለገሉ ነው’ ይላሉ።”

10ከእንግዲህ ስለማይመለስ፣

የተወለደባትንም ምድር ዳግመኛ ስለማያይ፣

ለተማረከው ንጉሥ አምርራችሁ አልቅሱ እንጂ፣

ቀድሞ ለሞተው አታልቅሱ፤ አትዘኑም።

11በአባቱ ምትክ በይሁዳ ላይ ስለ ነገሠው፣ ከዚህ ስፍራ በምርኮ ስለ ተወሰደው፣ ስለ ኢዮስያስ ልጅ ስለ ሰሎ22፥11 ኢዮአካዝ ተብሎም ይጠራል። እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ “ከእንግዲህ አይመለስም፤ 12ተማርኮ በሄደበት አገር ይሞታል እንጂ ይህችን ምድር ዳግመኛ አያይም።”

13“ቤተ መንግሥቱን በግፍ ለሚሠራ፣

ሰገነቱንም ፍትሕ በማዛባት ለሚገነባ፣

ወገኑን በነጻ ለሚያሠራ፣

የድካሙንም ዋጋ ለማይከፍለው፣

14‘ባለ ትልልቅ ሰገነት፣

ሰፊ ቤተ መንግሥት ለራሴ እሠራለሁ’ ለሚል ወዮለት!

ሰፋፊ መስኮቶችን ያበጅለታል፤

በዝግባ ዕንጨት ያስጌጠዋል፤

ቀይ ቀለምም ይቀባዋል።

15“በዝግባ ዕንጨት ብዛት፣

የነገሥህ ይመስልሃልን?

አባትህስ ፍትሕንና ጽድቅን በማድረጉ፣

የሚበላውና የሚጠጣው ጐድሎት ነበርን?

እነሆ፤ ሁሉም መልካም ሆነለት።

16የድኾችንና የችግረኞችን ፍትሕ አላጓደለም፤

ስለዚህም ሁሉ መልካም ሆነለት።

እኔን ማወቅ ማለት ይህ አይደለምን?”

ይላል እግዚአብሔር

17“የአንተ ዐይንና ልብ ያረፉት ግን፣

አጭበርብሮ ጥቅምን በማግኘት፣

የንጹሑን ደም በማፍሰስ፣

ጭቈናንና ግፍን በመሥራት ላይ ብቻ ነው።”

18ስለዚህ እግዚአብሔር ስለ ይሁዳ ንጉሥ ስለ ኢዮስያስ ልጅ ስለ ኢዮአቄም እንዲህ ይላል፤

“ ‘ዋይ ወንድሜ! ዋይ፣ እኅቴን!’

ብለው አያለቅሱለትም።

‘ዋይ፣ ጌታዬን! ዋይ፣ ለግርማዊነቱ!’

ብለውም አያለቅሱለትም።

19አህያ እንደሚቀበር ይቀበራል፤

ከኢየሩሳሌም በሮች ውጪ፤

ተጐትቶ ይጣላል።

20“ሊባኖስ ላይ ወጥተሽ ጩኺ፤

ድምፅሽን በባሳን አሰሚ፤

በዓባሪም ሆነሽ ጩኺ፤

ወዳጆችሽ ሁሉ ወድመዋልና።

21ተመችቶሽ በነበረ ጊዜ አስጠነቀቅሁሽ፤

አንቺ ግን፣ ‘አልሰማም’ አልሽ፤

ከትንሽነትሽ ጀምሮ መንገድሽ ይኸው ነበር፤

ቃሌንም አልሰማሽም።

22እረኞችሽ ሁሉ በነፋስ ይወሰዳሉ፤

ወዳጆችሽም ተማርከው ይሄዳሉ፤

ከክፋትሽም ሁሉ የተነሣ፣

ታፍሪያለሽ፤ ትዋረጂያለሽም።

23አንቺ፣ ‘በሊባኖስ’22፥23 ሊባኖስ የተባለው በኢየሩሳሌም ያለው ቤተ መንግሥት ነው (1ነገ 7፥23 ይመ)። ውስጥ የምትኖሪ፣

መኖሪያሽን በዝግባ ዛፍ የሠራሽ ሆይ፤

ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣

መከራ በላይሽ ሲመጣ ጩኸትሽ እንዴት ይሆን!

24“በሕያውነቴ እምላለሁ”፤ ይላል እግዚአብሔር “የይሁዳ ንጉሥ የኢዮአቄም ልጅ ኢኮንያን22፥24 በዕብራይስጥ ኮንያ ሲሆን የኢዮአኪን አቻ ስም ቃል ነው፤ 28 ይመ። የቀኝ እጄ የቀለበት ማኅተም ብትሆን እንኳ ኖሮ፣ አውልቄ እጥልሃለሁ፤ 25ሕይወትህን ለሚሿት፣ ለምትፈራቸው ለባቢሎናውያንና22፥25 ወይም ከለዳውያን ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደነፆር አሳልፌ እሰጥሃለሁ። 26አንተንና የወለደችህን እናትህን ወዳልተወለዳችሁበት ወደ ሌላ አገር ወርውሬ እጥላችኋለሁ፤ በዚያም ትሞታላችሁ። 27ልትመለሱባት ወደ ምትናፍቋት ምድር ከቶ አትመለሱም።”

28ይህ ኢኮንያን የተባለ ሰው፣ የተናቀና የተሰበረ ገንቦ፣

ማንም የማይፈልገው ዕቃ ነውን?

እርሱና ልጆቹ ለምን ወደ ውጪ ተጣሉ?

ወደማያውቁትስ ምድር ለምን ተወረወሩ?

29ምድር ሆይ፤ አንቺ ምድር፣ አንቺ ምድር፤

የእግዚአብሔርን ቃል ስሚ!

30እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“አንድ እንኳ የረባ ዘር የማይወጣለት፣

አንድ እንኳ በዳዊት ዙፋን የሚቀመጥ፣

ወይም በይሁዳ የሚገዛ የማይኖረው ነውና፤

በሕይወት ዘመኑ የማይከናወንለት፣

መካን ሰው ብላችሁ መዝግቡት።”