罗马书 16 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

罗马书 16:1-27

介绍菲比

1现在我给你们推荐我们的姊妹菲比,她是坚革哩教会的女执事。 2请你们因为在主里的关系,照着做圣徒的本分接待她。无论她有什么需要,请你们帮助她,因为她帮助过许多人,也帮助过我。

问候圣徒

3请代我问候百基拉亚居拉夫妇,他们是我在基督耶稣里的同工, 4为了救我将生死置之度外。不但我感谢他们,就是外族人的教会也感谢他们。 5请问候在他们家中聚会的教会。请问候我所爱的以拜尼土,他在亚细亚最先信主。 6请问候玛丽亚。她为你们受尽了劳苦。 7请问候安多尼古犹尼亚,他们是我的亲人,曾与我一同坐牢,同受患难,在使徒中很有名望,比我先信基督。 8请问候我在主里所爱的暗伯利9请问候在基督里与我同工的耳巴奴和我所爱的士大古10请问候亚比利,他在基督里曾受过考验。请问候亚利多布全家。 11请问候我的亲戚希罗天。请问候拿其数家中的信徒。 12请问候土非娜土富撒,她们都为主劳苦。请问候我所爱的彼息,她为主多受劳苦。 13请问候主所拣选的鲁孚,也问候他的母亲,他的母亲就是我的母亲。 14请问候亚逊其土弗勒干黑米八罗巴黑马和他们当中的其他弟兄姊妹。 15请问候非罗罗古犹利亚尼利亚和他的妹妹、阿林巴和他们那里的众圣徒。 16你们要以圣洁的吻彼此问候。基督的众教会都问候你们。

提防悖逆者

17弟兄姊妹,我劝你们要留意那些制造分裂、设置障碍、背离你们所学之道的人,你们要避开他们。 18他们并不是在事奉我们的主基督,只是为了满足自己的欲望,用花言巧语欺骗单纯善良的人。 19你们对主的顺服已人人皆知,我为你们高兴,我希望你们在好事上聪明,在坏事上无知。 20赐平安的上帝快要把撒旦践踏在你们脚下了。愿我们主耶稣的恩典常与你们同在!

其他人的问候

21我的同工提摩太和我的亲属路求耶孙所西巴德问候你们。 22我这为保罗代笔写信的德特在主里问候你们。 23接待我也接待全教会的该犹问候你们。 24主管本城财政的以拉都问候你们,括土弟兄也问候你们。

25感谢上帝!祂能使你们刚强,正如我所传讲的福音和耶稣基督的教导。这福音是自古隐藏、从未显明的奥秘, 26如今按着永恒上帝的命令,借着先知们所写的经书公诸于世,让世人都信从耶稣基督。 27愿荣耀借着耶稣基督归于独一全智的上帝,直到永远。阿们!

New Amharic Standard Version

ሮሜ 16:1-27

የግል ሰላምታ

1በክንክራኦስ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ16፥1 ወይም ዲያቈን የሆነችውን እኅታችንን ፌቤንን ዐደራ እላችኋለሁ። 2ለቅዱሳን ተገቢ በሆነው አቀባበል በጌታ እንድትቀበሏትና ከእናንተም የምትፈልገውን ማንኛውንም ርዳታ እንድታደርጉላት አሳስባችኋለሁ፤ ለብዙ ሰዎችና ለእኔም ጭምር ታላቅ ድጋፍ ነበረችና።

3በክርስቶስ ኢየሱስ አብረውኝ ለሚያገለግሉት ለጵርስቅላና16፥3 በግሪኩ ጰርስቃ የጵርስቅላ ተለዋጭ ስም ነው። ለአቂላ ሰላምታ አቅርቡልኝ። 4እነርሱም ለእኔ ሲሉ ሕይወታቸውን ለዐደጋ አጋልጠው ሰጡ፤ እኔ ብቻ ሳልሆን የአሕዛብ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ያመሰግኗቸዋል።

5በእነርሱ ቤት ላለች ቤተ ክርስቲያንም ሰላምታ አቅርቡልኝ።

ከእስያ አገር ለመጀመሪያ ወደ ክርስቶስ ለተመለሰው፣ ለወዳጄ ለአጤኔጦን ሰላምታ አቅርቡልኝ።

6ለእናንተ ብዙ ለደከመችው ለማርያ ሰላምታ አቅርቡልኝ።

7ከእኔ ጋር ታስረው ለነበሩት ዘመዶቼ ለአንዲራኒቆንና ለዩልያን ሰላምታ አቅርቡልኝ፤ እነርሱ በሐዋርያት መካከል ስመጥሮችና በክርስቶስ በማመንም እኔን የቀደሙ ናቸው።

8በጌታ ለምወድደው ለጵልያጦን ሰላምታ አቅርቡልኝ።

9በክርስቶስ አብሮን ለሚሠራው ለኢሩባኖንና ለውድ ወዳጄ ለስንጣክን ሰላምታ አቅርቡልኝ።

10በክርስቶስ ያለው እምነቱ ተፈትኖ ለተመሰገነው ለኤጤሌን ሰላምታ አቅርቡልኝ፤

ከአርስጣባሉ ቤተ ሰብ ለሆኑትም ሰላምታ አቅርቡልኝ።

11ለዘመዴ ለሄሮድዮና ሰላምታ አቅርቡልኝ፤

በጌታ ላሉት ለንርቀሱ ቤተ ሰቦች ሰላምታ አቅርቡልኝ።

12በጌታ ሆነው በትጋት ለሚሠሩት ሴቶች፣ ለፕሮፊሞናና ለጢሮፊሞሳ ሰላምታ አቅርቡልኝ።

በጌታ ሆና እጅግ ለደከመችው ለሌላዋ ሴት፣ ለተወደደችው ለጠርሲዳ ሰላምታ አቅርቡልኝ።

13በጌታ ለተመረጠው ለሩፎንና የእኔም እናት ለሆነችው ለእናቱ ሰላምታ አቅርቡልኝ።

14ለአስቀሪጦንና ለአፍለሶንጳ፣ ለሄሮሜን፣ ለጳጥሮባን፣ ለሄርማን፣ ከእነርሱም ጋር ላሉት ወንድሞች ሰላምታ አቅርቡልኝ።

15ለፍሌጎን፣ ለዩልያ፣ ለኔርያና ለእኅቱ፣ እንዲሁም ለአልንጦን፣ ከእነርሱም ጋር ላሉት ቅዱሳን ሰላምታ አቅርቡልኝ።

16በተቀደሰ አሳሳም ሰላምታ ተሰጣጡ።

የክርስቶስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።

17ወንድሞች ሆይ፤ መለያየትን ከሚፈጥሩትና የተማራችሁትን ትምህርት በመቃወም በጕዟችሁ መሰናክል ከሚያደርጉት እንድትጠነቀቁ አሳስባችኋለሁ፤ ከእነርሱም ራቁ። 18እንደ እነዚህ ያሉት ሰዎች የሚያገለግሉት ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ሳይሆን የራሳቸውን ሆድ ነው። በለሰለሰ አንደበታቸውና በሽንገላ የዋሆችን ያታልላሉ። 19የእናንተን ታዛዥነት ሁሉም ሰምተዋል፤ በዚህም እኔ እጅግ ተደስቻለሁ። ሆኖም በጎ ስለ ሆነው ነገር ጥበበኞች፣ ክፉ ስለ ሆነውም የዋሆች እንድትሆኑ እፈልጋለሁ።

20የሰላም አምላክ፣ ሰይጣንን ከእግራችሁ በታች ፈጥኖ ይቀጠቅጠዋል።

የጌታችን የኢየሱስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።

21አብሮኝ የሚሠራው ጢሞቴዎስ፣ እንዲሁም ዘመዶቼ የሆኑት ሉቂዮስ፣ ኢያሶንና ሱሲጴጥሮስ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።

22ይህን መልእክት የጻፍሁት እኔ ጤርጥዮስ፣ በጌታ ሰላምታ አቀርብላችኋለሁ።

23በመልካም መስተንግዶው እኔና በዚህ የምትገኘዋ መላዋ ቤተ ክርስቲያን ደስ የምንሰኝበት ጋይዮስ፣ ሰላምታ ያቀርብላችኋል።

የከተማዪቱ ግምጃ ቤት ሹም የሆነው ኤርስጦስ፣ ወንድማችንም ቍአስጥሮስ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።

24የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን፤ አሜን።16፥24 ቍጥር 24 የሚገኘው በአንዳንድ ቅጆች ብቻ ነው።

25-26በዘላለማዊ አምላክ ትእዛዝ ሕዝቦች ሁሉ አምነው እንዲታዘዙ፣ በነቢያት መጻሕፍት አሁን በተገለጠው፣ ላለፉት ረዥም ዘመናት ተሰውሮ በነበረው ምስጢር መገለጥ መሠረት፣ በአስተማርሁት ወንጌልና በኢየሱስ ክርስቶስ መሰበክ ሊያጸናችሁ ለሚችለው፣ 27እርሱ ብቻ ጥበበኛ ለሆነ አምላክ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።