约翰福音 17 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

约翰福音 17:1-26

耶稣的祷告

1耶稣说完后,就抬头望着天说:“父啊!时候到了,愿你使你的儿子得荣耀,好让你的儿子也使你得荣耀。 2因为你把管理世人的权柄赐给了祂,使祂可以将永生赐予你交托给祂的人。 3这永生就是,认识你——独一的真神,并且认识你所差来的耶稣基督。 4我已经完成你交给我的工作,使你在地上得了荣耀。 5父啊,现在让我和你同享创世以前我们所共有的荣耀吧!

6“你从世上赐给我的人,我已将你17:6 ”希腊文是“你的名”,“名”代表一个人的全部。显明给他们。他们本来属于你,你将他们赐给了我,他们遵守你的道。 7如今他们知道,你赐给我的一切都是从你那里来的, 8因为我已经把你赐给我的道赐给他们,他们也接受了,并且确实知道我是从你那里来的,也相信是你差遣了我。

9“我不为世人祈求,却为他们祈求,就是为你赐给我的那些人祈求,因为他们属于你。 10一切属于我的都是你的,属于你的也是我的,我从他们身上得了荣耀。 11现在我要离开这个世界去你那里了,他们却仍然留在世上。圣父啊,求你为了自己的名,就是你赐给我的名而保守他们,使他们像我们一样合而为一。 12我和他们在一起的时候,靠着你赐给我的名保守他们,看顾他们。除了那个注定灭亡的人以外,他们一个也没有灭亡,这是为了应验圣经上的话。

13“现在我要去你那里了,我趁着还在世上的时候这样说,是要叫他们心里充满我的喜乐。 14我已将你的道赐给他们,世人恨他们,因为他们像我一样不属于这个世界。 15我不求你带他们离开这个世界,但求你保守他们脱离那恶者。 16因为他们像我一样不属于这个世界。 17求你用真理,就是你的道,使他们圣洁。 18你怎样差我到世上来,我也照样差他们到世人中间。 19为了他们,我献上自己,使他们借着真理可以圣洁。

20“我不但为这些人祈求,也为那些因他们的话而信我的人祈求, 21使他们都合而为一,正如父你在我里面,我在你里面一样,并且使他们也在我们里面,好让世人相信是你差我来的。 22我又将你赐给我的荣耀赐给他们,使他们像我们一样合而为一。 23我在他们里面,你在我里面,好使他们也完完全全地合而为一。这样,世人便知道我是你差来的,而且知道你爱他们,就像爱我一样。

24“父啊!我在哪里,愿你赐给我的人也在哪里,好让他们看见你赐给我的荣耀,因为在创世以前你已经爱我了。 25公义的父啊!世界还未认识你以前,我已经认识你了,这些人也知道是你差我来的。 26我使他们认识了你的名,我还要使他们更认识你,好让你对我的爱存在他们里面,我也在他们里面。”

New Amharic Standard Version

ዮሐንስ 17:1-26

ኢየሱስ ስለ ራሱ መጸለዩ

1ኢየሱስ ይህን ከተናገረ በኋላ፣ ወደ ሰማይ ቀና ብሎ እንዲህ ሲል ጸለየ፤

“አባት ሆይ፤ ጊዜው ደርሷል፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ ልጅህን አክብረው፤ 2ከአንተ ለተቀበላቸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት እንዲሰጥ፣ በሰው ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥተኸዋልና። 3እውነተኛ አምላክ የሆንኸውን አንተንና የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት። 4የሰጠኸኝን ሥራ በመፈጸም በምድር አከበርሁህ። 5እንግዲህ አባት ሆይ፤ ዓለም ሳይፈጠር ከአንተ ጋር በነበረኝ ክብር በአንተ ዘንድ አክብረኝ።

ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ጸለየ

6“ለእነዚህ ከዓለም ለሰጠኸኝ ሰዎች ስምህን ገልጬላቸዋለሁ። የአንተ ነበሩ ለእኔ ሰጠኸኝ፤ እነርሱም ቃልህን ጠብቀዋል። 7የሰጠኸኝ ሁሉ ከአንተ እንደ ሆነ አሁን ዐውቀዋል፤ 8ምክንያቱም የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸው ተቀብለዋል፤ እኔም ከአንተ እንደ ወጣሁ በርግጥ ዐውቀዋል፤ አንተ እንደ ላክኸኝም አምነዋል፤ 9እነርሱ የአንተ ስለሆኑ እጸልይላቸዋለሁ፤ ለሰጠኸኝና የአንተ ለሆኑት እንጂ ለዓለም አልጸልይም። 10የእኔ የሆነው ሁሉ የአንተ ነው፤ የአንተ የሆነውም ሁሉ የእኔ ነው፤ በእነርሱም ከብሬአለሁ። 11ከእንግዲህ እኔ በዓለም አልቈይም፤ እነርሱ ግን በዓለም ውስጥ ናቸው፤ እኔም ወደ አንተ መምጣቴ ነው። ቅዱስ አባት ሆይ፤ እኛ አንድ እንደ ሆንን፣ እነርሱም አንድ እንዲሆኑ በሰጠኸኝ በስምህ ጠብቃቸው። 12እኔ ከእነርሱ ጋር ሳለሁ፣ በሰጠኸኝ ስም ከለልኋቸው፤ ጠበቅኋቸውም፤ የመጽሐፍ ቃል እንዲፈጸም ከአንዱ ከጥፋት ልጅ በቀር ከእነርሱ ማንም አልጠፋም።

13“አሁን ወደ አንተ መምጣቴ ነው፤ ነገር ግን ደስታዬ በእነርሱ ዘንድ የተሟላ እንዲሆን፣ አሁን በዓለም እያለሁ ይህን እናገራለሁ። 14ቃልህን ሰጥቻቸዋለሁ፤ እኔ ከዓለም እንዳይደለሁ፣ እነርሱም ከዓለም ባለመሆናቸው ዓለም ጠልቷቸዋል። 15የምለምንህም ከክፉው እንድትጠብቃቸው እንጂ፣ ከዓለም እንድታወጣቸው አይደለም። 16እኔ ከዓለም እንዳልሆንሁ ሁሉ፣ እነርሱም ከዓለም አይደሉም። 17ቃልህ እውነት ነው፤ በእውነትህ ቀድሳቸው17፥17 በግሪኩ ሀጊያዞ የሚለው ቅዱስ ለሆነ ተግባር መለየት ወይም መቀደስ ማለት ነው፤ 19 ይመ 18አንተ ወደ ዓለም እንደ ላክኸኝ እኔም ወደ ዓለም ልኬአቸዋለሁ። 19እነርሱ በእውነት የተቀደሱ እንዲሆኑ፣ ራሴን ስለ እነርሱ ቀድሻለሁ።”

ኢየሱስ ለአማኞች ሁሉ ጸለየ

20“የእነርሱን ትምህርት ተቀብለው በእኔ ለሚያምኑ ጭምር እንጂ ለእነዚህ ብቻ አልጸልይም፤ 21ይህም፣ አባት ሆይ፤ አንተ በእኔ፣ እኔም በአንተ እንዳለሁ ሁሉም አንድ እንዲሆኑ፣ እንዲሁም አንተ እኔን እንደ ላክኸኝ ዓለም ያምን ዘንድ፣ እነርሱም በእኛ እንዲሆኑ ነው። 22እኛ አንድ እንደ ሆንን እነርሱም አንድ እንዲሆኑ፣ የሰጠኸኝን ክብር ሰጥቻቸዋለሁ። 23ይህም እኔ በእነርሱ፣ አንተም በእኔ መሆንህ ነው። አንተ እንደ ላክኸኝና እኔን በወደድኸኝ መጠን እነርሱንም እንደ ወደድሃቸው ዓለም ያውቅ ዘንድ፣ አንድነታቸው ፍጹም ይሁን።

24“አባት ሆይ፤ እነዚህ የሰጠኸኝ፣ እኔ ባለሁበት እንዲሆኑ ዓለም ሳይፈጠር ስለ ወደድኸኝ የሰጠኸኝንም ክብሬን እንዲያዩ እፈልጋለሁ።

25“ጻድቅ አባት ሆይ፤ ዓለም ባያውቅህም፣ እኔ ዐውቅሃለሁ፤ እነዚህም አንተ እንደ ላክኸኝ ያውቃሉ። 26ለእኔ ያለህ ፍቅር በእነርሱ እንዲሆን፣ እኔም በእነርሱ እንድሆን፣ አንተን እንዲያውቁ17፥26 በግሪኩ ስምህን እንዲያወቁ ይላል። አድርጌአለሁ፤ እንዲያውቁህም አደርጋለሁ።”