约伯记 36 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

约伯记 36:1-33

1以利户又说:

2“再给我片刻,容我讲明,

我还有话替上帝说。

3我要旁征博引,

证明我的创造主公义。

4我的话绝非虚言,

知识全备者在你身旁。

5“上帝有大能,但不藐视人,

祂无所不知。

6祂不容恶人活命,

祂为穷苦人申冤。

7祂时时看顾义人,

使他们与君王同坐宝座,

永远受尊崇。

8他们若被锁链捆绑,

被苦难的绳索缠住,

9祂就会指明他们的所作所为,

让他们知道自己狂妄的罪愆。

10祂开启他们的耳朵,使之受教,

督促他们离开罪恶。

11他们若听从、事奉祂,

就可一生幸福,安享天年。

12否则,他们必死于刀下,

在无知中灭亡。

13不信上帝的人心存愤怒,

被上帝捆绑也不求救。

14他们盛年丧命,

与庙中的男妓一同夭亡。

15上帝借苦难拯救受苦的人,

借患难开通他们的耳朵。

16祂也要引领你脱离困境,

进入广阔自由之地,

使你享受满桌佳肴。

17“但恶人应受的审判落在你身上,

你难逃审判和惩罚。

18当心,不可因愤怒而嘲骂,

不可因赎金大就偏离正道。

19难道你呼求、使出浑身力气,

就能脱离困境吗?

20不要渴望黑夜来临——

就是众民被毁灭的时候。

21当心,不可转向罪恶,

因你喜欢罪恶胜于苦难。

22看啊,上帝的能力无以伦比。

谁能像祂那样赐人教诲?

23谁能为祂指定道路?

谁能说祂行事不义?

24人们都歌唱祂的作为,

你也要记得颂扬。

25祂的作为,万民都已看见,

世人从远处目睹。

26我们无法明白上帝的伟大,

祂的年岁无法数算。

27祂吸取水滴,

使之在云雾中化为雨,

28从云端沛然降下,

滋润人间。

29谁能明白云层的铺展,

及祂幔幕发出的雷声?

30祂在四围铺展闪电,

照亮大海的深处。

31祂借此治理万民,

赐下丰富的食物。

32祂手握闪电,

令它射向目标。

33雷声显明祂的作为,

就连牲畜也能察觉。

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 36:1-33

1ኤሊሁ በመቀጠል እንዲህ አለ፤

2“በእግዚአብሔር ፈንታ ሆኜ የምለው አለኝ፤

ጥቂት ታገሠኝና እነግርሃለሁ።

3ዕውቀቴን ከሩቅ አመጣለሁ፤

ፈጣሪዬ ጻድቅ እንደ ሆነ እገልጻለሁ።

4ቃሌ ሐሰት እንዳልሆነ አረጋግጣለሁ፤

በዕውቀቱ ፍጹም የሆነ ሰው ከአንተ ጋር ነው።

5“እግዚአብሔር ኀያል ነው፤ ግን ማንንም አይንቅም፤

ኀያል፣ በዐላማውም ጽኑ ነው።

6ክፉዎችን በሕይወት አያኖርም፤

ለተቸገሩት ግን በቅን ይፈርዳል።

7ዐይኖቹን ከጻድቃን ላይ አያነሣም፤

ከነገሥታት ጋር በዙፋን ላይ ያስቀምጣቸዋል፤

ለዘላለምም ከፍ ከፍ ያደርጋቸዋል።

8ነገር ግን ሰዎች በሰንሰለት ቢታሰሩ፣

በመከራም ገመድ ቢጠፈሩ፣

9በእብሪት የፈጸሙትን በደል፣

ተግባራቸውን ይነግራቸዋል።

10ተግሣጽን እንዲሰሙ ያደርጋቸዋል፤

ከክፋታቸውም እንዲመለሱ ያዝዛቸዋል።

11ታዝዘው ቢያገለግሉት፣

ቀሪ ዘመናቸውን በተድላ፣

ዕድሜያቸውንም በርካታ ይፈጽማሉ።

12ባይሰሙ ግን፣

በሰይፍ36፥12 ወይም፣ ወንዙን ያቋርጣሉ ይጠፋሉ፤

ያለ ዕውቀትም ይሞታሉ።

13“ልባቸው ከእግዚአብሔር የራቀ፣ ቍጣን ያስተናግዳሉ፤

በሰንሰለት ባሰራቸውም ጊዜ እንኳ ወደ እርሱ አይጮኹም።

14በቤተ ጣዖት ውስጥ ዝሙት በሚፈጽሙት መካከል፣

ገና በወጣትነታቸው ይቀጫሉ።

15ነገር ግን የሚሠቃዩትን ከሥቃያቸው ያድናቸዋል፤

በመከራቸውም ውስጥ ይናገራቸዋል።

16“አንተንም ከመከራ መንጋጋ፣

ጭንቀት ወደሌለበት ወደ ሰፊ ስፍራ፣

ምርጥ ምግብ ወደ ሞላበት ማእድ ያወጣሃል።

17አሁን ግን ለክፉዎች የሚገባው ፍርድ በላይህ ተጭኗል፤

ፍርድና ብይን ይዘውሃል።

18ባለጠግነት እንዳያታልልህ፣

የእጅ መንሻ ብዛትም እንዳያስትህ ተጠንቀቅ።

19ባለጠግነትህም ሆነ ብርቱ ጥረትህ ሁሉ፣

ችግር ውስጥ እንዳትገባ ሊረዳህ ይችላልን?

20ሰዎች ከቤታቸው36፥20 በዕብራይስጥ ከ18-20 ያለው ክፍል ትርጕሙ በትክክል አይታወቅም። የሚወሰዱበትን፣

ሌሊት አትመኝ።

21ከመከራ ይልቅ መርጠኸዋልና፣

ወደ ክፋት እንዳትመለስ ተጠንቀቅ።

22“እነሆ፤ እግዚአብሔር በኀይሉ ከፍ ከፍ ብሏል፤

እንደ እርሱስ ያለ አስተማሪ ማን ነው?

23እርሱን መንገድ የሚመራው፣

ወይም ‘ይህን አጥፍተሃል’ የሚለው ማን ነው?

24ሰዎች በመዝሙር ያወደሱትን፣

የእርሱን ሥራ ማወደስ አትዘንጋ።

25ሰው ሁሉ አይቶታል፤

ሰዎችም በትኵረት ተመልክተውታል።

26እነሆ፤ እግዚአብሔር ከአእምሯችን በላይ ታላቅ ነው!

የዘመኑም ቍጥር ከመታወቅ ያልፋል።

27“የውሃን ነጠብጣብ ወደ ላይ ያተንናል፤

መልሶም በዝናብ መልክ በጅረቶች ላይ ያወርዳል፤

28ደመናት ጠል ያንጠባጥባሉ፤

ዶፍም በሰው ላይ ይወርዳል።

29ደመናትን እንዴት እንደሚዘረጋ፣

ከድንኳኑም እንዴት እንደሚያንጐደጕድ ሊረዳ የሚችል ማን ነው?

30መብረቁን በዙሪያው እንዴት እንደሚበትን ተመልከት፤

የባሕሩንም ወለል ይሸፍናል።

31እርሱ ሕዝብን የሚያስተዳድረው፣36፥31 ወይም፣ የሚያስተዳድረው ምግብንም አትረፍርፎ የሚሰጣቸው

በዚህ መንገድ ነው።

32እጆቹን በመብረቅ ይሞላቸዋል፤

ዒላማውንም እንዲመታ ያዝዘዋል።

33ነጐድጓዱ ውሽንፍር እንደሚከተለው ያመለክታል፤

ከብቶችም እንኳ መምጣቱን ይጠቍማሉ።