约伯记 30 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

约伯记 30:1-31

哀叹今日的痛苦

1“但如今,比我年少的人竟嘲笑我,

他们的父亲曾被我鄙视,

连我的牧羊犬都不如。

2他们精力衰竭,

对我有何益处?

3他们贫穷饥饿,瘦弱不堪,

夜间在干旱荒凉之地啃食。

4他们在草丛中拔咸草充饥,

以罗腾树根为食。

5他们被赶离人群,

像贼一样被喝斥。

6他们只好住在荒谷,

在地洞和岩穴栖身;

7在杂草间嚎叫如兽,

在树丛中蜷缩一团。

8他们是愚昧无名之辈,

被人用鞭子赶出境外。

9“如今,他们竟唱歌讽刺我,

我成了他们的笑柄。

10他们厌恶我,不愿靠近我,

任意朝我脸上吐唾沫。

11因为上帝苦待我,使我毫无力量,

他们才在我面前肆无忌惮。

12这些无赖从右边攻击我,

迫使我逃亡,

他们展开攻势要毁灭我。

13他们截断我的路,

想方设法害我,无人相助。

14他们冲破防线,

从废墟中向我袭来。

15恐惧笼罩着我,

我的尊荣随风而去,

我的荣华如云消散。

16“如今我的生命将尽,

痛苦的日子抓住我。

17夜间我的骨头刺痛,

如被啃噬,无休无止。

18上帝猛力抓住我的衣服,

紧紧地揪住我的衣领。

19祂把我扔进淤泥,

使我如尘埃灰烬。

20“上帝啊!我向你呼求,你不回应;

我站起来,你也不理睬。

21你变得对我残酷无情,

用你大能的手迫害我,

22把我提到风中,让我被风吹走,

被暴风抛来抛去。

23我知道你要带我去死亡之地,

那是你为众生所定的归宿。

24“诚然,不幸的人在困境中呼救,

无人会伸手加害他。

25难道我不曾为受苦的人哭泣,

我的心不曾为穷困者悲伤吗?

26我盼望幸福,来的却是灾祸;

我期待光明,来的却是黑暗。

27我心里一直烦乱不安,

苦难的日子迎面袭来。

28我皮肤发黑,不是因为日晒,

我在会众中站起来呼救。

29我成了豺狼的兄弟,

驼鸟的伙伴。

30我的皮肤发黑、脱落,

我的骨头如被烤焦。

31我的琴唱出哀乐,

我的箫奏出悲鸣。

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 30:1-31

1“አሁን ግን በዕድሜ ከእኔ የሚያንሱ፣

ከመንጋዬ ጠባቂ ውሾች ጋር እንዳይቀመጡ፣

አባቶቻቸውን የናቅኋቸው፣

እነዚህ ይሣለቁብኛል።

2ጕልበት የከዳቸው፣

የክንዳቸው ብርታት ምን ፋይዳ ይሞላልኝ ነበር?

3ከችጋርና ከራብ የተነሣ ጠወለጉ፤

ሰው በማይኖርበት በረሓ፣

በደረቅም ምድር በሌሊት ተንከራተቱ።30፥3 ወይም ተሠቃዩ

4ከቍጥቋጦ ምድር ጨው ጨው የሚል አትክልት ለቀሙ፤

ምግባቸውም የክትክታ ሥር ነበር።

5ከኅብረተ ሰቡ ተለይተው ተባረሩ፤

ሰዎች እንደ ሌባ ይጮኹባቸዋል።

6በዐለት መካከል በምድር ጕድጓድ፣

በደረቅ ሸለቆ ዋሻ ውስጥ ለመኖር ተገደዱ።

7በጫካ ውስጥ ያናፋሉ፤

በእሾኻማ ቍጥቋጦ መካከልም ይታፈጋሉ።

8ስማቸው የማይታወቅ አልባሌ ናቸው፤

ከምድሪቱም ተባርረዋል።

9“አሁን ግን ልጆቻቸው በዘፈን ይሣለቁብኛል፤

በእነርሱም ዘንድ መተረቻ ሆኛለሁ።

10ይጸየፉኛል፣ ወደ እኔም አይቀርቡም፤

ያለ ምንም ይሉኝታ በፊቴ ይተፋሉ።

11እግዚአብሔር የቀስቴን አውታር ስላላላውና በመከራም ስለ መታኝ፣

በፊቴ መቈጠብን ትተዋል።

12በቀኜ በኩል ባለጌዎች30፥12 በዕብራይስጥ የዚህ ቃል ትርጕም በትክክል አይታወቅም። ሆ! ብለው ተነሡብኝ፤

ለእግሬም ወጥመድ ዘረጉ፤

የዐፈር ድልድልም አዘጋጁብኝ።

13መንገድ ዘጉብኝ፤

የሚገታቸው30፥13 ወይም ማንም ሊረዳው አይችልም አሉ። ሳይኖር፣

ሊያጠፉኝ ተነሡ።

14በሰፊ ንቃቃት ውስጥ እንደሚመጣ ሰው መጡብኝ፤

በፍርስራሽም መካከል እየተንከባለሉ ደረሱብኝ።

15በድንጋጤ ተውጫለሁ፤

ክብሬ በነፋስ እንደሚወሰድ ተወስዷል፤

በሰላም መኖሬም እንደ ደመና እልም ብሎ ጠፍቷል።

16“አሁን ነፍሴ በውስጤ ዐለቀች፤

የመከራ ዘመንም ይዞኛል።

17ደዌ በሌሊት ዐጥንቴን ይበሳል፤

የሚቈረጥመኝም ፋታ አይሰጠኝም።

18እግዚአብሔር በታላቅ ኀይሉ ልብሴን30፥18 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ዕብራይስጡ ግን፣ እንደ ልብስ ሆኖብኛል ይላል። ጨምድዷል፤

በልብሴም ክሳድ ዐንቆ ይዞኛል።

19እርሱ ጭቃ ውስጥ ጥሎኛል፤

እኔም ከዐፈርና ከዐመድ አልተሻልሁም።

20“እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ ጮኽሁ፤ ነገር ግን አልመለስህልኝም፤

በፊትህም ቆምሁ፤ አንተ ግን ዝም አልኸኝ።

21ተመልሰህ ጨካኝ ሆንህብኝ፤

በክንድህም ብርታት አስጨነቅኸኝ።

22ወደ ላይ ነጥቀህ በነፋስ ፊት አበረርኸኝ፤

በዐውሎ ነፋስም ወዲያ ወዲህ ወዘወዝኸኝ።

23ለሕያዋን ሁሉ ወደ ተመደበው ስፍራ፣

ወደ ሞት እንደምታወርደኝ ዐውቃለሁ።

24“የተጐዳ ሰው ተጨንቆ ድረሱልኝ ብሎ ሲጮኽ፣

በርግጥ ክንዱን የሚያነሣበት ማንም የለም።

25በመከራ ውስጥ ላሉት አላለቀስሁምን?

ለድኾችስ ነፍሴ አላዘነችምን?

26ነገር ግን መልካም ስጠብቅ፣ ክፉ ነገር ደረሰብኝ፤

ብርሃንንም ስጠባበቅ፣ ጨለማ መጣብኝ።

27በውስጤ ያለው ነውጥ አላቋረጠም፤

የመከራ ዘመንም መጣብኝ።

28በፀሓይ አይደለም እንጂ፣ ጠቋቍሬ እዞራለሁ፤

በጉባኤ መካከል ቆሜ ለርዳታ እጮኻለሁ።

29የቀበሮች ወንድም፣

የጕጕቶችም ባልንጀራ ሆኛለሁ።

30ቈዳዬ ጠቍሮ ተቀረፈ፤

ዐጥንቴም በትኵሳት ነደደ።

31በገናዬ ለሐዘን፣

እንቢልታዬም ለልቅሶ ተቃኝቷል።