约伯记 22 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

约伯记 22:1-30

以利法再次回答

1提幔以利法回答说:

2“人对上帝能有何益处?

即使智者对祂又有何益?

3全能者岂会因你为人公义而喜悦,

因你行为纯全而获利?

4祂岂会因你敬虔而惩罚你、审判你?

5你岂不是罪恶深重,

过犯无数?

6你无故强取弟兄的物品作抵押,

剥去贫寒者的衣服。

7你不给口渴的人水喝,

不给饥饿的人食物。

8土地归了权贵,

只让显要占有。

9你让寡妇空手而去,

你打断孤儿的臂膀。

10因此你周围布满网罗,

恐惧突然笼罩你。

11黑暗遮掩你的视线,

洪水淹没你。

12“上帝岂不在高天之上吗?

看,天上的星宿何其高远!

13你却说,‘上帝知道什么?

祂怎能隔着幽暗施行审判?

14当祂在穹苍巡弋时,

密云挡住祂的视线。’

15难道你要走恶人的古道,

步他们的后尘?

16他们死期未到便已夭逝,

他们的根基被洪涛卷走。

17他们对上帝说,‘离开我们吧!

全能者能把我们怎么样?’

18然而,是上帝把美物充满他们的家;

因此,我决不苟同他们的想法。

19义人看见他们的结局便欢喜,

无辜者见了便嘲笑,

20说,‘我们的仇敌果然被铲除,

他们的财产已被火吞噬。’

21“你要顺从上帝,与祂和好,

福乐就会临到你。

22你要接受祂的教诲,

把祂的话谨记在心。

23你若归向全能者,就必得到恢复。

你若将罪恶从帐篷中远远赶走,

24将金子扔进尘土,

俄斐的金子丢在布满石头的溪谷,

25全能者必成为你的金子,

成为你珍贵的银子。

26那时,你必从全能者那里找到欢乐,

你必抬头仰望上帝。

27你向祂祷告,祂必垂听,

你必向祂还所许的愿。

28你想做的事都会成功,

必有光照亮你的道路。

29人遭贬抑时,你说,‘使他们升高吧。’

上帝就会拯救他们,

30祂甚至会解救有罪之人,

他们必因你的手清洁而获救。”

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 22:1-30

ኤልፋዝ

1ቴማናዊውም ኤልፋዝ እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“ሰው እግዚአብሔርን ሊጠቅም ይችላልን?

ጠቢብ እንኳ ቢሆን ምን ይጠቅመዋል?

3አንተ ጻድቅ ብትሆን ሁሉን የሚችለውን አምላክ ምን ደስ ታሰኘዋለህ?

መንገድህ ያለ ነቀፋ ቢሆንስ የሚተርፈው ምንድን ነው?

4“እርሱ የሚገሥጽህ፣

ፍርድ ቤትም የሚያቀርብህ ስለምትፈራው ነውን?

5ክፋትህ ታላቅ፣

ኀጢአትህ ፍጻሜ የሌለው አይደለምን?

6ያለ አንዳች ምክንያት ከወንድሞችህ መያዣ ወስደሃል፤

ሰዎችን ገፍፈህ፣ ያለ ልብስ ዕራቍታቸውን አስቀርተሃል።

7የዛሉትን ውሃ አላጠጣህም፤

የተራቡትንም ምግብ ከልክለሃል።

8ባለ ርስትና ኀያል፣

በእርሱም የምትኖር ክቡር ሰው ብትሆንም፣

9መበለቶችን ባዶ እጃቸውን ሰድደሃል፤

የድኻ ዐደጎችንም ክንድ ሰብረሃል።

10ድንገተኛ አደጋ ያናወጠህ፣

ወጥመድም ዙሪያህን የከበበህ ለዚህ ነው።

11እንዳታይ ጨለማ የሆነብህ፣

ጐርፍም ያጥለቀለቀህ ለዚህ ነው።

12“እግዚአብሔር ከፍ ባለው ሰማይ የሚኖር አይደለምን?

በሩቅ ከፍታ ያሉትን ከዋክብት ያያል!

13ይህም ሆኖ ሳለ እንዲህ አልህ፤ ‘እግዚአብሔር ምን ያውቃል?

በእንዲህ ያለ ጨለማ ውስጥስ ይፈርዳልን?

14በሰማይ ክበብ ላይ ሲራመድ፣

እንዳያየን ጥቅጥቅ ያለ ደመና ይሸፍነዋል።’

15ኀጢአተኞች በሄዱባት፣

በጥንቷ መንገድ እንደ ተመላለስህ ትቀራለህን?

16ጊዜያቸው ሳይደርስ ተነጠቁ፤

መሠረታቸውም በጐርፍ ተወሰደ።

17እግዚአብሔርንም ‘አትድረስብን!

ሁሉን የሚችል አምላክም ምን ያደርግልናል?’ አሉ።

18ቤታቸውን በመልካም ነገር የሞላው ግን እርሱ ነው፤

ስለዚህ ከኀጢአተኞች ምድር እርቃለሁ።

19“ጻድቃንም የእነዚያን ጥፋት አይተው ይደሰታሉ፤

ንጹሓንም እንዲህ ብለው ያፌዙባቸዋል፤

20‘በርግጥ ጠላቶቻችን ጠፍተዋል፤

ሀብታቸውም በእሳት ተበልቷል።’

21“ለእግዚአብሔር ተገዛ፤ ከእርሱም ጋር ሰላም ይኑርህ፤

በረከትም ታገኛለህ።

22ምክርን ከአፉ ተቀበል፤

ቃሉንም በልብህ አኑር።

23ሁሉን ወደሚችል አምላክ ብትመለስ ትጠገናለህ፤

ክፋትን ከድንኳንህ ብታርቅ፣

24የወርቅህን አንኳር ትቢያ ላይ፣

የኦፊር ወርቅህንም ጥልቅ ሸለቆ ውስጥ ብትጥለው፣

25ሁሉን ቻዩ አምላክ ወርቅ ይሆንልሃል፤

ምርጥ ብር ይሆንልሃል።

26በዚያ ጊዜ ሁሉን በሚችል አምላክ ደስ ይልሃል፤

ፊትህንም ወደ እግዚአብሔር ታቀናለህ።

27ወደ እርሱ ትጸልያለህ፤ እርሱም ይሰማሃል፤

አንተም ስእለትህን ትሰጣለህ።

28ያሰብኸው ይከናወንልሃል፤

በመንገድህም ላይ ብርሃን ይበራል።

29ሰዎች ቢዋረዱና አንተ፣ ‘ከፍ አድርጋቸው’ ብትል፣

እርሱ ዝቅ ያሉትን ያድናል፤

30በጎ ያልሆነውን ሰው እንኳ፣

ከአንተ እጅ ንጽሕና የተነሣ ያድነዋል።”