箴言 29 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

箴言 29:1-27

1屡教不改、顽固不化者,

必突然灭亡,无可挽救。

2义人增多,万众欢腾;

恶人得势,万民叹息。

3爱慕智慧的使父亲欢欣,

结交妓女的必耗尽钱财。

4君王秉公行义,国家安定;

他若收受贿赂,国必倾倒。

5奉承邻舍,等于设网罗绊他。

6恶人被自己的罪缠住,

义人却常常欢喜歌唱。

7义人关心穷人的冤屈,

恶人对此漠不关心。

8狂徒煽动全城,

智者平息众怒。

9智者跟愚人对簿公堂,

愚人会怒骂嬉笑不止。

10嗜杀之徒憎恶纯全无过的人,

但正直的人保护他们29:10 但正直的人保护他们”或译“索取正直人的性命”。

11愚人尽发其怒,

智者忍气含怒。

12君王若听谗言,

臣仆必成奸徒。

13贫穷人和欺压者有共同点:

他们的眼睛都是耶和华所赐。

14君王若秉公审判穷人,

他的王位必永远坚立。

15管教之杖使孩子得智慧,

放纵的子女让母亲蒙羞。

16恶人当道,罪恶泛滥;

义人必得见他们败亡。

17好好管教儿子,

他会带给你平安和喜乐。

18百姓无神谕便任意妄为,

但遵守律法的人必蒙福。

19管教仆人不能单靠言语,

因为他虽明白却不服从。

20言语急躁的人,

还不如愚人有希望。

21主人若从小就娇惯仆人,

他终必成为主人的麻烦。

22愤怒的人挑起纷争,

暴躁的人多有过犯。

23骄傲的人必遭贬抑,

谦卑的人必得尊荣。

24与盗贼为伍是憎恶自己,

他即使发誓也不敢作证。

25惧怕人的必自陷网罗,

信靠耶和华的必安稳。

26许多人讨君王的欢心,

但正义伸张靠耶和华。

27为非作歹,义人厌恶;

行为正直,恶人憎恨。

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 29:1-27

1ከብዙ ተግሣጽ በኋላ ዐንገቱን የሚያደነድን ሰው፣

በድንገት ይጠፋል፤ መዳኛም የለውም።

2ጻድቃን ሥልጣን ሲይዙ ሕዝብ ሐሤት ያደርጋል፤

ክፉዎች ሲገዙ ግን ሕዝብ ያቃስታል።

3ጥበብን የሚወድድ ሰው አባቱን ደስ ያሰኛል፤

የአመንዝራዎች ወዳጅ ግን ሀብቱን ያባክናል።

4ፍትሕን በማስፈን ንጉሥ አገርን ያረጋጋል፤

ጕቦ ለማግኘት የሚጐመጅ ግን ያፈራርሳታል።

5ባልንጀራውን የሚሸነግል፣

ለገዛ እግሩ መረብ ይዘረጋል።

6ክፉ ሰው በራሱ ኀጢአት ይጠመዳል፤

ጻድቅ ግን ይዘምራል፤ ደስም ይለዋል።

7ጻድቅ ለድኾች ፍትሕ ይጨነቃል፤

ክፉ ሰው ግን ደንታ የለውም።

8ተሳዳቢዎች ከተማን ያውካሉ፤

ጠቢባን ግን ቍጣን ያበርዳሉ።

9ጠቢብ ሰው ከተላላ ጋር ወደ ሸንጎ ቢሄድ፣

ተላላ ይቈጣል፤ ያፌዛል፤ ሰላምም አይኖርም።

10ደም የተጠሙ ሰዎች ሐቀኛን ሰው ይጠላሉ፤

ቅን የሆነውንም ለመግደል ይሻሉ።

11ተላላ ሰው ቍጣውን ያለ ገደብ ይለቅቀዋል፤

ጠቢብ ሰው ግን ራሱን ይቈጣጠራል።

12ገዥ የሐሰት ወሬ የሚሰማ ከሆነ፣

ሹማምቱ ሁሉ ክፉዎች ይሆናሉ።

13ድኻውና ጨቋኙ የጋራ ነገር አላቸው፤

እግዚአብሔር ለሁለቱም የዐይን ብርሃንን ሰጥቷቸዋል።

14ንጉሥ ለድኻ ትክክለኛ ፍርድ ቢሰጥ፣

ዙፋኑ ዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

15የተግሣጽ በትር ጥበብን ታጐናጽፋለች፤

መረን የተለቀቀ ልጅ ግን እናቱን ያሳፍራል።

16ክፉዎች ሥልጣን ሲይዙ ኀጢአት ይበዛል፤

ጻድቃን ግን የእነርሱን ውድቀት ያያሉ።

17ልጅህን ቅጣው፤ ሰላም ይሰጥሃል፤

ነፍስህንም ደስ ያሰኛታል።

18ራእይ በሌለበት ሕዝብ መረን ይሆናል፤

ሕግን የሚጠብቅ ግን የተባረከ ነው።

19አገልጋይ በቃል ብቻ ሊታረም አይችልም፤

ቢያስተውለውም እንኳ በጀ አይልም።

20በችኰላ የሚናገርን ሰው ታያለህን?

ከእርሱ ይልቅ ተላላ ተስፋ አለው።

21ሰው አገልጋዩን ከልጅነቱ ጀምሮ ቢያቀማጥል፣

የኋላ ኋላ ሐዘን29፥21 በዕብራይስጡ የዚህ ቃል ትርጓሜ በርግጠኝነት አይታወቅም። ያገኘዋል።

22ቍጡ ሰው ጠብን ይጭራል፤

ግልፍተኛም ብዙ ኀጢአት ይሠራል።

23ሰውን ትዕቢቱ ያዋርደዋል፤

ትሑት መንፈስ ያለው ግን ክብርን ይጐናጸፋል።

24የሌባ ግብረ አበር የገዛ ራሱ ጠላት ነው፤

የመሐላውን ርግማን እየሰማ ጭጭ ይላል።

25ሰውን መፍራት ወጥመድ ነው፤

በእግዚአብሔር የሚታመን ግን በሰላም ይኖራል።

26ብዙዎች በገዥ ፊት ተደማጭነት ማግኘት ይሻሉ፤

ሰው ፍትሕ የሚያገኘው ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

27ጻድቃን አታላዮችን ይጸየፋሉ፤

ክፉዎችም ቅኖችን ይጠላሉ።