箴言 23 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

箴言 23:1-35

1你若与官长同席,

要注意面对的是谁。

2如果你是贪吃的人,

就要节制食欲23:2 节制食欲”希伯来文是“把刀放在喉咙上”。

3不可贪恋他的美食,

这美食是圈套。

4别为钱财耗尽心力,

要明智,适可而止。

5钱财眨眼之间消逝无踪,

它必长出翅膀如鹰飞去。

6不要吃吝啬人的饭,

不可贪图他的美味。

7因为他总是精于算计,

嘴上说“请吃,请喝”,

心里却另有盘算。

8你必呕出所吃的那点饭,

你说的美言都必枉费。

9不要和愚人说话,

他必藐视你的智言。

10不可挪移古时的界石,

不可侵占孤儿的田地。

11因他们的救赎主强大,

祂必对付你,替他们申冤。

12你要专心接受教诲,

侧耳倾听智言。

13不要疏于管教孩子,

杖责不会使他毙命,

14杖责能救他脱离死亡。

15孩子啊,

你若心里有智慧,

我心里也会欢喜。

16你的口若说正直的话,

我的内心也欢畅不已。

17不要心里羡慕罪人,

要终日敬畏耶和华。

18这样,你必前途光明,

你的盼望不会幻灭。

19孩子啊,听我的话,

要有智慧,心守正道。

20不要结交酒肉朋友,

21因为好酒贪吃者必穷困,

贪睡的人必穿破衣烂衫。

22要听从生养你的父亲,

不可轻视年老的母亲。

23要买真理、智慧、教诲和悟性,

不可卖掉。

24义人的父亲喜乐无限,

智慧之子使父母欢欣。

25你要使父母快乐,

叫生你的人欢欣。

26孩子啊,把你的心交给我,

欢然走我的道路。

27妓女是深坑,淫妇是陷阱;

28她像强盗般埋伏,

使世间增添奸徒。

29谁有灾祸?谁有忧伤?

谁有争吵?谁有怨言?

谁无故受伤?谁两眼发红?

30就是那些沉迷醉乡,

品尝醇和之酒的人!

31虽然鲜红的酒在杯中闪烁,

喝下去痛快,但不要盯着它。

32它终必像蛇一样伤你,

像毒蛇一样咬你。

33你的眼会看见怪异的景象,

你会神智不清,胡言乱语。

34你好像躺在怒海中,

又像卧在桅杆顶上。

35你会说:“人打我,我不痛;

人揍我,我不知。

什么时候醒了,再干一杯!”

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 23:1-35

1ከገዥ ጋር ለመብላት በምትቀመጥበት ጊዜ፣

በፊትህ ያለውን በሚገባ23፥1 ወይም ማን መሆኑን አስተውል፤

2ስግብግብም ብትሆን እንኳ፣

በጕረሮህ ላይ ካራ አጋድምበት፤

3የእርሱ ጣፋጭ መብል አያስጐምጅህ፤

ምግቡ አታላይ ነውና።

4ሀብት ለማግኘት ስትል ራስህን አታድክም፤

ሐሳብህን የመግታት ጥበብ ይኑርህ።

5በሀብት ላይ ዐይንህን ብትጥል፣

ወዲያው ይጠፋል፤

ወደ ሰማይ እንደሚበርር ንስር፣ በርግጥ ክንፍ አውጥቶ ይበርራል።

6የሥሥታምን ምግብ አትብላ፤

ጣፋጭ መብሉም አያስጐምጅህ፤

7ሁልጊዜ ስለ ዋጋ የሚያሰላ ሰው ነውና፤23፥7 ወይም በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና ወይም ግብዣ አዘጋጅቶ

“ብላ፣ ጠጣ” ይልሃል፤

ልቡ ግን ከአንተ ጋር አይደለም።

8የበላሃት ትንሿ እንኳ ታስመልስሃለች፤

የምስጋና ቃልህንም ከንቱ ታደርጋለህ።

9ከጅል ጋር አትነጋገር፤

የቃልህን ጥበብ ያንኳስሳልና።

10የጥንቱን የወሰን ምልክት አታፋልስ፤

አባት የሌላቸውንም ልጆች መሬት አትግፋ፤

11ታዳጊያቸው ብርቱ ነውና፤

እርሱ ይፋረድላቸዋል።

12ልብህን ለምክር፣

ጆሮህንም ለዕውቀት ቃል ስጥ።

13ልጅን ከመቅጣት ወደ ኋላ አትበል፤

በአርጩሜ ብትገርፈው አይሞትም።

14በአርጩሜ ቅጣው፤

ነፍሱንም ከሞት23፥14 ዕብራይስጡ ሲኦል ይላል አድናት።

15ልጄ ሆይ፤ ልብህ ጠቢብ ቢሆን፣

የእኔም ልብ ሐሤት ያደርጋል፤

16ከንፈሮችህ ትክክሉን ቢናገሩ፣

ውስጣዊ ሁለንተናዬ ሐሤት ያደርጋል።

17ልብህ በኀጢአተኞች አይቅና፤

ነገር ግን ዘወትር እግዚአብሔርን ለመፍራት ትጋ።

18ለነገ ርግጠኛ አለኝታ ይኖርሃል፤

ተስፋህም ከንቱ አይሆንም።

19ልጄ ሆይ አድምጥ፤ ጠቢብም ሁን፤

ልብህም ከትክክለኛው መንገድ አይውጣ።

20ብዙ የወይን ጠጅ ከሚጠጡ፣

ሥጋ ከሚሰለቅጡ ጋር አትወዳጅ፤

21ሰካራሞችና ሆዳሞች ድኾች ይሆናሉና፤

እንቅልፋምነትም ቡትቶ ያለብሳቸዋል።

22የወለደህን አባትህን አድምጥ፤

እናትህንም ባረጀች ጊዜ አትናቃት።

23እውነትን ግዛት እንጂ አትሽጣት፤

ጥበብን፣ ተግሣጽንና ማስተዋልን ገንዘብህ አድርግ።

24የጻድቅ ሰው አባት እጅግ ደስ ይለዋል፤

ጠቢብ ልጅ ያለውም በእርሱ ሐሤት ያደርጋል።

25አባት እናትህ ደስ ይበላቸው፤

ወላጅ እናትህም ሐሤት ታድርግ።

26ልጄ ሆይ፤ ልብህን ስጠኝ፤

ዐይኖችህም ከመንገዴ አይውጡ፤

27ዘልዛላ ሚስት ጠባብ ጕድጓድ፣

አመንዝራም ሴት ዐዘቅት ናትና፤

28እንደ ወንበዴ ታደባለች፤

በሰዎችም መካከል ወስላቶችን ታበዛለች።

29ዋይታ የማን ነው? ሐዘንስ የማን ነው?

ጠብ የማን ነው? ብሶትስ የማን ነው?

በከንቱ መቍሰል የማን ነው? የዐይን ቅላትስ የማን ነው?

30የወይን ጠጅ በመጠጣት ጊዜያቸውን ለሚያባክኑ ነው፤

እየዞሩ ድብልቅ የወይን ጠጅ ለሚቀማምሱ ሰዎች ነው።

31መልኩ ቀይ ሆኖ፣

በብርጭቆ ውስጥ ሲያንጸባርቅ፣

ሰተት ብሎ በሚወርድበትም ጊዜ፣ ወደ ወይን ጠጅ ትክ ብለህ አትመልከት።

32በመጨረሻው እንደ እባብ ይነድፋል፤

እንደ እፉኝትም መርዙን ይረጫል።

33ዐይኖችህ እንግዳ ነገር ያያሉ፤

አእምሮህም ይቀባዥራል።

34በባሕር ላይ የተኛህ፣

በመርከብ ምሰሶ ጫፍ ላይ የተጋደምህ ትመስላለህ።

35አንተም፣ “መቱኝ፤ አልተጐዳሁም፤

ደበደቡኝ፤ አልተሰማኝም፤

ታዲያ፣ ሌላ መጠጥ እንዳገኝ፣

መቼ ነው የምነቃው?” ትላለህ።