箴言 22 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

箴言 22:1-29

1美名胜过巨富,

恩宠比金银宝贵。

2富人和穷人相同:

都由耶和华所造。

3明哲人遇祸躲避,

愚昧人前往受害。

4心存谦卑、敬畏耶和华,

必得财富、尊荣和生命。

5奸徒之道有荆棘和陷阱,

想保全生命的必须远避。

6教导孩童走正路,

他到老也不偏离。

7富人管辖穷人,

欠债的是债主的仆人。

8播种不义的必收灾祸,

他的恶势力终必瓦解。

9慷慨的人必蒙福,

因他给穷人食物。

10赶走嘲讽者,纷争平息,

争吵和羞辱也会消除。

11喜爱清心、口吐恩言的人,

必与君王为友。

12耶和华的眼目护卫真理,

祂必推翻奸徒的言论。

13懒惰人说:“外面有狮子,

我会丧命街头。”

14淫妇的口是深坑,

耶和华憎恶的人必陷进去。

15愚昧缠住孩童的心,

教棍能远远赶走它。

16靠压榨穷人敛财和送礼给富人的,

都必穷困潦倒。

智者之言

17你要侧耳听智者之言,

专心领受我的教诲,

18铭记在心、随时诵咏,

方为美事。

19今天我将这些指示你,

为要使你倚靠耶和华。

20关于谋略和知识,

我已写给你三十条,

21要使你认识真理,

能准确答复差你来的人。

22不可仗势剥削贫穷人,

法庭上不可欺凌弱者,

23因为耶和华必为他们申冤,

夺去掠夺他们之人的性命。

24不可结交脾气暴躁者,

不要跟易怒之人来往,

25免得你沾染他们的恶习,

不能自拔。

26不要为人击掌作保,

不要为欠债的抵押。

27如果你还不起,

连你的床也会被抬走。

28不可移动祖先定下的界石。

29你看那精明能干的人,

他必侍立在君王面前,

不会效力于泛泛之辈。

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 22:1-29

1መልካም ስም ከብዙ ብልጽግና ይመረጣል፤

መከበርም ከብርና ከወርቅ ይበልጣል።

2ባለጠጋና ድኻ የሚጋሩት ነገር፣

እግዚአብሔር የሁላቸውም ፈጣሪ መሆኑ ነው።

3አስተዋይ ሰው አደጋ ሲያይ መጠጊያ ይሻል፤

ብስለት የጐደለው ግን በዚያው ይቀጥላል፤ መከራም ያገኘዋል።

4ትሕትናና እግዚአብሔርን መፍራት፣

ሀብትን፣ ክብርንና ሕይወትን ያስገኛል።

5በክፉዎች መንገድ ላይ እሾኽና ወጥመድ አለ፤

ነፍሱን የሚጠብቅ ግን ከእነዚህ ይርቃል።

6ልጅን የሚሄድበትን መንገድ አስተምረው፤22፥6 ወይም አስጀምረው

በሚሸመግልበት ጊዜ ከዚያ ፈቀቅ አይልም።

7ባለጠጋ ድኻን ይገዛል፤

ተበዳሪም የአበዳሪ ባሪያ ነው።

8ክፋትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፤

የቍጣውም በትር ይጠፋል።

9ቸር ሰው ራሱ ይባረካል፤

ምግቡን ከድኾች ጋር ይካፈላልና።

10ፌዘኛን አስወጣው፤ ጠብ ይወገዳል፤

ጥልና ስድብም ያከትማል።

11የልብ ንጽሕናን ለሚወድድና ንግግሩም ሞገስ ላለው ሰው፣

ንጉሥ ወዳጁ ይሆናል።

12የእግዚአብሔር ዐይኖች ዕውቀትን ይጠብቃሉ፤

የማይታመኑትን ሰዎች ቃል ግን እርሱ ከንቱ ያደርጋል።

13ሰነፍ፣ “አንበሳ ውጭ አለ፤

መንገድ ላይ እገደላለሁ” ይላል።

14የአመንዝራ ሴት አፍ ጥልቅ ጕድጓድ ነው፤

እግዚአብሔር የተቈጣውም ይገባበታል።

15ሞኝነት በሕፃን ልብ ታስሯል፤

የተግሣጽ በትር ግን ከእርሱ ያርቅለታል።

16ሀብቱን ለማካበት ድኻን የሚበድል፣

ለባለጠጋም ስጦታ የሚያቀርብ፣ ሁለቱም ይደኸያሉ።

የጠቢባን ምክር

17የጠቢባንን ቃል ልብ ብለህ ስማ፤

ልብህም ወደ ትምህርቴ ያዘንብል፤

18በልብህ ስትጠብቃቸው፣

ሁሉም በከንፈሮችህ ላይ የተዘጋጁ ሲሆኑ ደስ ይላልና።

19ስለዚህ እምነትህ በእግዚአብሔር ላይ እንዲሆን፣

ዛሬ አንተን ራስህን አስተምርሃለሁ።

20የምክርና የዕውቀት ቃል የሆኑ፣

መልካም ትምህርቶችን22፥20 ወይም ሠላሳ ትምህርቶችን አልጻፍሁልህምን?

21ለላከህ ተገቢውን መልስ ትሰጥ ዘንድ፣

እውነተኛና የታመኑ ቃሎችን እንዳስተምርህ አይደለምን?

22ድኾች በመሆናቸው ብቻ ድኾችን አትበዝብዛቸው፤

ችግረኛውንም በአደባባይ አታንገላታው፤

23እግዚአብሔር ይፋረድላቸዋልና፤

የሚቀሟቸውንም ይቀማቸዋል።

24ከግልፍተኛ ጋር ወዳጅ አትሁን፤

በቀላሉ ቱግ ከሚልም ሰው ጋር አትወዳጅ፤

25አለዚያ መንገዱን ትማራለህ፤

ራስህም ትጠመድበታለህ።

26በዋስትና ቃል እጅ አትምታ፤

ለብድር ተያዥ አትሁን፤

27የምትከፍለው ካጣህ፣

የምትተኛበት ዐልጋ ከሥርህ ይወሰድብሃል።

28የቀድሞ አባቶችህ ያስቀመጡትን፣

የጥንቱን የወሰን ምልክት አታፋልስ።

29በሙያው ሥልጡን የሆነውን ሰው አይተሃልን?

በነገሥታት ዘንድ ባለሟል ይሆናል፤

አልባሌ ሰዎችን አያገለግልም።