箴言 13 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

箴言 13:1-25

1智慧儿听从父训,

嘲讽者不听责备。

2口出良言尝善果,

奸徒贪行残暴事13:2 奸徒贪行残暴事”或译“奸徒必饱受虐待”。

3说话谨慎,可保性命;

口无遮拦,自取灭亡。

4懒惰人空有幻想,

勤快人心想事成。

5义人憎恶虚谎,

恶人行事可耻。

6公义守卫正直的人,

邪恶倾覆犯罪之徒。

7有人强充富有,

其实身无分文;

有人假装贫穷,

却是腰缠万贯。

8富人用财富赎命,

穷人却免受惊吓。

9义人的光灿烂,

恶人的灯熄灭。

10自高自大招惹纷争,

虚心受教才是睿智。

11不义之财必耗尽,

勤俭积蓄财富增。

12盼望无期,使人忧伤;

夙愿得偿,带来生机13:12 带来生机”希伯来文是“使人像棵生命树”。

13蔑视训言,自招灭亡;

敬畏诫命,必得赏赐。

14智者的训言是生命之泉,

可使人避开死亡的网罗。

15睿智使人蒙恩惠,

奸徒之路通灭亡。

16明哲知而后行,

愚人炫耀愚昧。

17奸恶的使者陷入灾祸,

忠诚的使者带来医治。

18不受管教的贫穷羞愧,

接受责备的受到尊崇。

19愿望实现使心甘甜,

远离恶事为愚人憎恶。

20与智者同行必得智慧,

与愚人结伴必受亏损。

21祸患追赶罪人,

义人必得善报。

22善人为子孙留下产业,

罪人给义人积聚财富。

23穷人的田地出产丰富,

因不公而被抢掠一空。

24不用杖管教儿女是憎恶他们,

疼爱儿女的随时管教他们。

25义人丰衣足食,

恶人食不果腹。

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 13:1-25

1ጠቢብ ልጅ የአባቱን ምክር በማስተዋል ይሰማል፤

ፌዘኛ ግን ተግሣጽን አያዳምጥም።

2ሰው ከከንፈሩ ፍሬ መልካም ነገር ያገኛል፤

ወስላቶች ግን ዐመፅን ይናፍቃሉ።

3አንደበቱን የሚጠብቅ ሕይወቱን ይጠብቃል፤

አፉ እንዳመጣለት የሚናገር ግን ይጠፋል።

4ሰነፍ አጥብቆ ይመኛል፤ አንዳችም አያገኝም፤

የትጉሆች ምኞት ግን ይረካል።

5ጻድቅ ሐሰትን ይጠላል፤

ክፉ ሰው ግን ኀፍረትንና ውርደትን ያመጣል።

6ጽድቅ ቅን የሆነውን ሰው ትጠብቀዋለች፤

ክፋት ግን ኀጢአተኛውን ትጥለዋለች።

7ምንም ሳይኖረው ባለጠጋ መስሎ የሚታይ ሰው አለ፤

ሌላው ድኻ መስሎ ይታያል፤ ግን ብዙ ሀብት አለው።

8የሰው ሀብቱ ለሕይወቱ ቤዛ ሊሆነው ይችላል፤

ድኻው ግን ሥጋት የለበትም።

9የጻድቃን ብርሃን ደምቆ ይበራል፤

የክፉዎች መብራት ግን ይጠፋል።

10ትዕቢት ጠብን ብቻ ያስፋፋል፤

ጥበብ ግን ምክርን በሚቀበሉ ዘንድ ትገኛለች።

11ያላግባብ የተገኘ ገንዘብ እየተመናመነ ያልቃል፤

ገንዘቡን ጥቂት በጥቂት የሚያከማች ግን ይጠራቀምለታል።

12ለነገ የሚባል ተስፋ ልብን ያሳምማል፤

የተሳካ ምኞት ግን የሕይወት ዛፍ ነው።

13ምክርን የሚያቃልል በራሱ ላይ ጥፋት ያመጣል፤

ትእዛዝን የሚያከብር ግን ወሮታን ይቀበላል።

14የጠቢብ ትምህርት የሕይወት ምንጭ ናት፤

ሰውን በሞት ወጥመድ እንዳይያዝ ታደርገዋለች።

15መልካም ማስተዋል ሞገስን ታስገኛለች፤

የከዳተኞች መንገድ ግን አስቸጋሪ ነው።13፥15 ወይም የከዳተኞች መንገድ ግን አይጸናም

16አስተዋይ ሰው ሥራውን በዕውቀት ያከናውናል፤

ተላላ ግን ሞኝነቱን ይገልጣል።

17ክፉ መልእክተኛ መከራ ውስጥ ይገባል፤

ታማኝ መልእክተኛ ግን ፈውስን ያመጣል።

18ተግሣጽን የሚንቅ ወደ ድኽነትና ኀፍረት ይሄዳል፤

ዕርምትን የሚቀበል ሁሉ ግን ይከበራል።

19ምኞት ስትፈጸም ነፍስን ደስ ታሰኛለች፤

ተላሎች ግን ከክፋት መራቅን ይጸየፋሉ።

20ከጠቢብ ጋር የሚሄድ ጠቢብ ይሆናል፤

የተላሎች ባልንጀራ ግን ጕዳት ያገኘዋል።

21መጥፎ ዕድል ኀጢአተኛን ይከታተላል፤

ብልጽግና ግን የጻድቃን ዋጋ ነው።

22ደግ ሰው ለልጅ ልጆቹ ውርስ ትቶ ያልፋል፤

የኀጢአተኞች ሀብት ግን ለጻድቃን ይከማቻል።

23የድኾች ዕርሻ የተትረፈረፈ ምርት ያስገኛል፤

የፍትሕ መጓደል ግን ጠራርጎ ይወስደዋል።

24በአርጩሜ ከመቅጣት የሚሳሳለት ልጁን ይጠላል፤

የሚወድደው ግን በጥንቃቄ ይቀጣዋል።

25ጻድቅ እስኪጠግብ ድረስ ይበላል፤

የክፉዎች ሆድ ግን እንደ ተራበ ይኖራል።