箴言 11 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

箴言 11:1-31

1耶和华憎恶骗人的天平,

喜爱公平的砝码。

2傲慢带来羞辱,

谦卑者有智慧。

3正直人靠诚实引导,

奸诈者被奸诈毁灭。

4在降怒之日,财富毫无益处,

唯有公义能救人免于死亡。

5纯全人行义走坦途,

恶人作恶致沉沦。

6正直人被义行所救,

奸诈者被私欲所掳。

7恶人一死,他的希望就破灭,

他对财势的冀望转眼成空。

8义人脱离患难,

恶人落入苦难。

9不敬虔的张口败坏邻舍,

义人却因知识获得拯救。

10义人亨通,全城快乐;

恶人灭亡,人人欢呼。

11城因正直人的祝福而兴盛,

因恶人的口舌而倾覆。

12无知者轻视邻舍,

明哲人保持缄默。

13嚼舌者泄露秘密,

忠信者守口如瓶。

14缺乏智谋,国必败亡;

谋士众多,战无不胜。

15为他人作保,必受亏损;

厌恶当保人,得享平安。

16贤淑的女子得到尊荣,

残暴的男子得到资财。

17仁慈的人造福自己,

残酷的人惹祸上身。

18恶人赚来的转眼成空,

播种公义的必获奖赏。

19坚持行义,必得生命;

追逐罪恶,终必灭亡。

20心术不正的人令耶和华憎恶,

纯全无过的人蒙耶和华喜爱。

21恶人终必落入法网,

义人的子孙必得拯救。

22女子貌美无内涵,

如同猪鼻挂金环。

23义人的愿望结出善果,

恶人的希望招致烈怒。

24有人乐善好施,反倒越来越富;

有人一毛不拔,反而越来越穷。

25慷慨好施的必得昌盛,

恩待他人的必蒙恩待。

26囤粮不卖,惹人咒诅;

乐意卖粮,必蒙祝福。

27寻求良善得恩惠,

追求罪恶遭祸患。

28倚仗财势者必衰败,

义人必兴旺如绿叶。

29祸害自家,必一无所有,

愚人必做智者的仆役。

30义人结果如生命之树,

智者深得人心。

31看啊!义人在世上尚且遭报11:31 义人在世上尚且遭报”七十士译本为“义人尚且难以得救”,参见彼得前书4:18

更何况罪人和恶人呢?

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 11:1-31

1እግዚአብሔር የተጭበረበረ ሚዛንን ይጸየፋል፤

ትክክለኛ መለኪያ ግን ደስ ያሰኘዋል።

2ትዕቢት ስትመጣ ውርደትም ትከተላለች፤

በትሑት ዘንድ ግን ጥበብ ትገኛለች።

3ቅኖችን ትክክለኛነታቸው ትመራቸዋለች፤

ወስላቶች ግን በገዛ አታላይነታቸው ይጠፋሉ።

4በቍጣ ቀን ሀብት ፋይዳ የለውም፤

ጽድቅ ግን ከሞት ትታደጋለች።

5ለፍጹማን ሰዎች ጽድቃቸው መንገዳቸውን ታቃናላቸዋለች፤

ክፉዎች ግን በገዛ ክፋታቸው ይወድቃሉ።

6ቅኖችን ጽድቃቸው ትታደጋቸዋለች፤

ወስላቶች ግን በክፉ ምኞታቸው ይጠመዳሉ።

7ክፉ ሰው ሲሞት ተስፋው ከንቱ ትሆናለች፤

በኀይሉ የተመካበትም ሁሉ እንዳልነበረ ይሆናል።

8ጻድቅ ከመከራ ይድናል፤

ይልቁን መከራው በክፉው ላይ ይደርሳል።

9ክፉ ሰው ባልንጀራውን በአፉ ያጠፋል፤

ጻድቃን ግን በዕውቀት ያመልጣሉ።

10ጻድቃን ሲሳካላቸው ከተማ ደስ ይላታል፤

ክፉዎች ሲጠፉ እልልታ ይሆናል።

11በቅኖች በረከት ከተማ ከፍ ከፍ ትላለች፤

በክፉዎች አንደበት ግን ትጠፋለች።

12ማመዛዘን የጐደለው ሰው ባልንጀራውን ያንኳስሳል፤

አስተዋይ ግን አንደበቱን ይገዛል።

13ሐሜተኛ ምስጢር አይጠብቅም፤

ታማኝ ሰው ግን ምስጢር ይጠብቃል።

14በአመራር ጕድለት መንግሥት ይወድቃል፤

የመካሮች ብዛት ግን ድልን ርግጠኛ ያደርጋል።

15ለማይታወቅ ሰው ዋስ የሚሆን መከራ ያገኘዋል፤

ዋስትና ለመስጠት እጅ የማይመታ ግን ምንም አይደርስበትም።

16ርኅሩኅ ሴት ክብር ታገኛለች፤

ጕልበተኛ ሰዎች ግን ብልጽግናን ብቻ ያገኛሉ።

17ደግ ሰው ራሱን ይጠቅማል፤

ጨካኝ ግን በራሱ ላይ መከራ ያመጣል።

18ክፉ ሰው የሚያገኘው ትርፍ መቅኖ የለውም፤

ጽድቅን የሚዘራ ግን አስተማማኝ ዋጋ ያገኛል።

19እውነተኛ ጻድቅ ሕይወትን ያገኛል፤

ክፋትን የሚከተል ግን ወደ ሞቱ ይጓዛል።

20እግዚአብሔር ልበ ጠማሞችን ይጸየፋል፤

በመንገዳቸው ነቀፋ በሌለባቸው ሰዎች ግን ደስ ይሰኛል።

21ክፉ ሳይቀጣ እንደማይቀር ዕወቅ፣

ጻድቃን ግን በነጻ ይሄዳሉ።

22በእርያ አፍንጫ ላይ እንደ ተሰካ የወርቅ ቀለበት፣

ማስተዋል የጐደላት ቈንጆ ሴት እንዲሁ ናት።

23የጻድቃን ምኞት ምንጊዜም ፍጻሜው ያማረ ነው፤

የክፉዎች ተስፋ ግን በቍጣ ያከትማል።

24አንዱ በለጋስነት ይሰጣል፤ ሆኖም ይበልጥ ያገኛል፤

ሌላው ያለ መጠን ይሰስታል፤ ግን ይደኸያል።

25ለጋስ ይበለጽጋል፤

ሌሎችን የሚያረካም ራሱ ይረካል።

26በድብቅ እህል የሚያከማቸውን ሕዝብ ይረግመዋል፤

አውጥቶ የሚሸጥ ግን በረከት ይጐናጸፋል።

27በጎ ነገርን ተግቶ የሚሻ በጎ ነገር ይጠብቀዋል፤

ክፉ ነገር የሚፈልገውን ግን ክፉ ያገኘዋል።

28በሀብቱ የሚታመን ሁሉ ይወድቃል፤

ጻድቃን ግን እንደ አረንጓዴ ቅጠል ይለመልማሉ።

29ቤተ ሰቡን የሚያውክ ሰው ነፋስን ይወርሳል፤

ተላላም ሰው የጠቢብ ሎሌ ይሆናል።

30የጻድቅ ፍሬ የሕይወት ዛፍ ናት፤

ነፍሳትን የሚማርክም ጠቢብ ነው።

31ጻድቃን ለሠሩት ሥራ በምድር የእጃቸውን የሚያገኙ ከሆነ፣

የክፉዎችና የኀጢአተኞችማ የቱን ያህል የባሰ ይሆን?