申命记 6 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

申命记 6:1-25

最大的诫命

1“你们的上帝耶和华吩咐我教导你们以下的诫命、律例和典章,以便你们在将要占领的土地上遵行。 2这样,你们就会得享长寿,你们及子孙就会终生敬畏你们的上帝耶和华,遵守祂借我吩咐你们的一切律例和诫命。 3以色列人啊,你们要留心听,谨慎遵行,以便你们在那奶蜜之乡可以凡事顺利、子孙众多,正如你们祖先的上帝耶和华给你们的应许。 4听啊,以色列人,耶和华是我们的上帝,耶和华是独一的。 5你们要全心、全意、全力爱你们的上帝耶和华。 6要将我今天吩咐你们的话牢记在心, 7并教导你们的儿女,无论在家在外,或起或卧,都要讲论这些律例和诫命。 8要把它们系在手上、戴在额上作记号, 9要写在城门上和自家的门框上。

10“你们的上帝耶和华将带你们进入祂向你们祖先亚伯拉罕以撒雅各起誓要赐给你们的土地。那里的宏伟城邑不是你们建造的, 11满屋的美物不是你们积攒的,井不是你们挖掘的,葡萄园和橄榄树也不是你们栽种的。你们在那里吃饱喝足之后, 12要小心,不可忘记把你们从受奴役之地——埃及救出来的耶和华。 13要敬畏你们的上帝耶和华,事奉祂,凭祂的名起誓。 14不可随从周围各族的神明, 15免得你们的上帝耶和华向你们发怒,把你们从世上消灭;因为祂住在你们当中,祂痛恨不贞。

16“不可像在玛撒那样试探你们的上帝耶和华。 17要谨遵你们的上帝耶和华吩咐你们的诫命、法度和律例。 18你们要做耶和华视为正与善的事,以便你们可以凡事顺利,得到耶和华起誓赐给你们祖先的佳美之地, 19赶出所有敌人,正如耶和华所言。

20“将来你们的子孙会问,‘我们的上帝耶和华给你们颁布这些法度、律例和典章是什么意思?’ 21你们要告诉他们,‘我们曾在埃及做法老的奴隶,耶和华用大能的手领我们离开埃及22我们亲眼看见耶和华行伟大而可畏的神迹奇事,惩罚埃及和法老全家。 23祂带领我们离开埃及,为要把我们带进祂起誓赐给我们祖先的这片土地。 24我们的上帝耶和华吩咐我们遵守这一切律例、敬畏祂,以便我们可以常常受益,生命无忧,正如今日的情形。 25如果我们按照我们的上帝耶和华的吩咐,在祂面前谨遵这一切诫命,我们便被算为义人。’

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 6:1-25

አምላክህን እግዚአብሔርን ውደድ

1ዮርዳኖስን ተሻግራችሁ በምትወርሷት ምድር እንድትጠብቁት አስተምራችሁ ዘንድ አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የሰጠኝ ትእዛዝ፣ ሥርዐትና ሕግ ይህ ነው፤ 2ይኸውም፣ የምሰጣችሁን ሥርዐቱንና ትእዛዙን ሁሉ በመጠበቅ፣ ዕድሜያችሁ እንዲረዝም፣ አንተ፣ ልጆችህና ከእነርሱ በኋላ የሚመጡት ልጆቻቸው በሕይወት ዘመናችሁ ሁሉ አምላካችሁን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) ትፈሩት ዘንድ ነው። 3እንግዲህ እስራኤል ሆይ ስማ፤ የአባቶችህ አምላክ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በሰጠህ ተስፋ መሠረት፣ ማርና ወተት በምታፈስሰው ምድር መልካም እንዲሆንልህና እጅግ እንድትበዛ፣ ትእዛዙንም ትጠብቅ ዘንድ ጥንቃቄ አድርግ።

4እስራኤል ሆይ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) አንድ እግዚአብሔር (ያህዌ) ነው6፥4 ወይም፣ እግዚአብሔር አምላካችን ነው፤ እግዚአብሔር አንድ ነው ወይም እግዚአብሔር አምላካችን ነው፤ እግዚአብሔር ብቻውን5አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም ኀይልህ ውደድ። 6ዛሬ የምሰጥህን እነዚህን ትእዛዞች በልብህ ያዝ። 7ለልጆችህም አስጠናቸው፤ በቤትህ ስትቀመጥ፣ በመንገድም ስትሄድ፣ ስትተኛና ስትነሣም ስለ እነርሱ ተናገር። 8በእጅህ ላይ ምልክት አድርገህ እሰራቸው፤ በግንባርህም ላይ ይሁኑ። 9በቤትህ መቃኖች በግቢህም በሮች ላይ ጻፋቸው።

10አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ለአንተ ለመስጠት ለአባቶችህ ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ ወደ ማለላቸው ምድር ሲያስገባህ፣ በዚያም ያልሠራሃቸውን ታላላቅና ያማሩ ከተሞችን፣ 11የራስህ ባልነበሩ መልካም ነገሮች ሁሉ የተሞሉ ቤቶችን፣ ያልቈፈርሃቸውን የውሃ ጕድጓዶች፣ ያልተከልሃቸውን የወይን ተክሎችና የወይራ ዛፎች ሲሰጥህና በልተህም ስትጠግብ፣ 12ከባርነት ምድር ከግብፅ ያወጣህን እግዚአብሔርን (ያህዌ) እንዳትረሳ ተጠንቀቅ!

13አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) ፍራ፤ እርሱን ብቻ አገልግል፤ በስሙም ማል። 14በዙሪያህ ያሉ ሕዝቦች የሚያመልኳቸውን ሌሎች አማልክት አትከተል፤ 15ምክንያቱም በመካከልህ ያለው አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ቀናተኛ አምላክ (ኤሎሂም) ስለሆነ፣ በአንተም ላይ ቍጣው ስለሚነድድ፣ ከምድር ገጽ ያጠፋሃል። 16በማሳህ እንዳደረጋችሁት አምላካችሁን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) አትፈታተኑት። 17አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የሰጣችሁን ትእዛዞች፣ መመሪያዎችና ሥርዐቶች በጥንቃቄ ጠብቁ። 18መልካም እንዲሆንልህና እግዚአብሔር (ያህዌ) ለአባቶችህ በመሐላ እንድትወርሳት፣ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ተስፋ የሰጣቸውን መልካሚቱን ምድር ገብተህ ቀናና መልካም የሆነውን አድርግ፤ 19እግዚአብሔር (ያህዌ) በተናገረው መሠረትም ጠላቶችህን ሁሉ ከፊትህ ታስወጣለህ። 20በሚመጡት ዘመናት ልጅህ፣ “አምላካችን እግዚአብሔር (ያህዌ ኤሎሂም) ያዘዛችሁ የመመሪያዎቹ፣ የሥርዐቶቹና የሕጎቹ ትርጕም ምንድን ነው?” ብሎ በሚጠይቅህ ጊዜ፣ 21እንዲህ በለው፤ “እኛ በግብፅ የፈርዖን ባሮች ነበርን፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ግን በብርቱ እጅ ከግብፅ አወጣን። 22እኛ በዐይናችን እያየን እግዚአብሔር (ያህዌ) ታላላቅና አስፈሪ የሆኑ ታምራዊ ምልክቶችና ድንቆችን በግብፅ፣ በፈርዖንና በመላው ቤተ ሰዎቹ ላይ አደረገ። 23እኛን ግን ለአባቶቻችን በመሐላ ተስፋ ወደ ሰጣቸው ምድር ሊያስገባንና ሊሰጠን ከዚያ አወጣን። 24ዛሬ እንደ ሆነው ሁሉ ምንጊዜም መልካም እንዲሆንልንና በሕይወት እንድንኖር ይህን ሥርዐት ሁሉ እንድንፈጽም፣ አምላካችንንም እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) እንድንፈራ እግዚአብሔር (ያህዌ) አዘዘን። 25እንግዲህ ይህን ሁሉ ሕግ እርሱ ባዘዘን መሠረት፣ በአምላካችን በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፊት ተጠንቅቀን ከጠበቅን፣ ያ ለእኛ ጽድቃችን ይሆናል።”